Time in Ethiopia:

Jun 30, 2014

ልቃዊነት የዘመናችን ሃይማኖት

ZETOBIA | Monday, June 30, 2014
 ካሣሁን ዓለሙ:-

ሃይማኖት በሥርዎ ቃሉ ማመንና መታመን የሚሉ ፅንሣተ-ሐሣብን የያዘ ቃል ነው፡፡ ማመን በአንድ ነገር ላይ እምነት ማሳደር ሲሆን መታመን ደግሞ ላመኑበት ነገር መታገልና መቆም ነው፡፡ ይህንን ይዘን ወደ ፍልስፍናው መከራከሪያ ስንገባ በዓለማችን የሚገኙ የሃይማኖት ይዘቶችን በሦስት ከፍለን ልንያቸው እንችላለን፡፡
1) በእግዚአብሔር ህልውነት ላይ የተመሠረተ ሃይማኖት (Theist)
የእግዚአብሔር ህልውነትን በማመንና እሱን በመመሥከር እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ጋር ግኑኝነት የሚያደርግ በሥራው ፍፁም የሆነ አምላክ መሆኑን ይቀበላል፡፡ ስለሆነም የሰው ልጆች ከእነሱ በላይና ፍጹም ከኾነ ኃይል ጋር ግንኙነት ያደርጋሉ፤ እሱም በመገለጥ ስለ ዐለማትና ፍጥረታት አፈጣጠር፣ ስለ ሰው ልጆች መፈጠርና ህልውና ነግሯቸዋል፤ ያነጋግራቸዋል ብሎ ያምና፤ ለዚህም ጥብቅና ቆሞ ይመሠክራል፤ ይከራከራል፡፡
2) በእግዚአብሔር አለመኖር ላይ የተመሠረተ ሃይማኖት (Atheist)
ይኸ የእግዚአብሔርን ህልውነት የሚክድና ለዚያም አቋም ጥብቅና የቆመ ሃይማኖት መሰል አስተምህሮ ነው፡፡ይህም ሃይማኖት የራሱ መታወቂያ አለው፡፡ በአንድ በኩል ሰይጣንን በግል እያመለከ የእግዚአብሔርን ህልውነት የሚቃወም ሲሆን በአብዛኛው በኢሉምናቲ የሚሥጢር ማኅበራት የሚቀነቀን ነው፤ ምሥጢራዊነቱም ያመዝናል፡፡ ስለዚህ በግልፅና በተቋማዊ አደረጃጀት የማይታወቅ ቢመስልም በአብዛኛው በሳይንስና በፍልስፍና አስተምህሮ ተወሽቆ እምነቱ ተቀባይነት አግኝቶ እንዲስፋፋ ጥረት ይደረግለታል፡፡ የዚህ ሃይማኖት አቀንቃኞች በዋናነትዝግመተ ለውጠኛችና ቁሳካላዊያን ናቸው፡፡ለምሳሌ እንደ ፈርደሪክ ኒቼ፣ ካርል ማርክስ፣ ሌኒን፣ ዳሪዊን፣ ሪቻርድ ዳውኪንስና መሰሎቻቸውን መጥቀስይ ቻላል፡፡
3) ‹አሊለም› (እግዚአብሔር አለ-የለም) ሃይማኖት (Agnostic)
የእዚህ ሃይማኖት መነሻው ልቃዊነት (Liberalism) ማሳለጫው ምንፍቅና (Skeptic) ተግባሩም ውል አልባነትና ግደለሽነት (indifference) ነው፡፡ የመከራከሪያ ስልቱም ዥዋዥዌ መጫወት ነው፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Ethiopian Sudani border Security tension flares again

Geez Bet | Monday, June 30, 2014
hartoum (HAN) June 30, 2014.  Regional Security border updates. The Horn of Africa’s Fractious neighbors renew crossfire over disputed border lines after a Sudan troops was killed in clashes with unknown Ethiopian forces.
“Ethiopian militia group opened unprovoked fire from across the border at Sudan border post , they fired mortars and automatic weapons,” one
Sudani Diplomat told HAN (the Horn of Africa Newsline) in Khartoum on condition of anonymity. “Our troops responded with retaliatory fire.”
ሙሉውን አንብብ-Read More

Why is Ethiopia the second poorest country on the planet? [Prof. Alemayehu G.Mariam]

Geez Bet | Monday, June 30, 2014
Recently, a well-known correspondent for one of the major American media outlets stationed in Ethiopia sent me an email grousing about my article urging boycott of Coca Cola in Ethiopia. He wrote, “I’m sorry to be blunt, but I don’t understand the thrust of this article [on boycotting Coca Cola]. You seem intent on misleading at least some of your ‘millions’ of readers that Ethiopian politics is simply evil regime vs angelic (and united) opponents.”

My response to the befuddled foreign correspondent was terse, swift and unapologetic. “It is. Deal with it! I am not sorry to be blunt. It is your right to mindlessly parrot the regime’s line!!!” When one’s journalistic accreditation and privileged existence in Ethiopia depends on one’s choice of words and reportorial insipidity, timidity masquerading as integrity and neutrality becomes a journalistic virtue.
I suspect this commentary on the question of poverty in Ethiopia will befuddle the ruling regime in Ethiopia, its cronies, supporters and domestic and foreign apologists.
ሙሉውን አንብብ-Read More

የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጥፋቱ ምንድን ነው? (በፐሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም)

Geez Bet | Monday, June 30, 2014
ቴዎድሮስ ካሣሁንን በአካል አላውቀውም፤  በዘፈንና በጭፈራ በእውነት ተደሳች መሆን ካቃተኝ ቆይቷል፤ ከ ኅዳር 1967 ጀምሮ ነው የቆረቆረኝ፤ ይህ ሰው እንደሰውና እንደ ኢትዮጲያዊ በየጊዜው የሚደርስበትን ወደ ግፍ የሚጠጋ በደል ስመለከት ያው የለመድነው ምቀኝነት ነው እያልሁ ሳልፈው ቆየሁ፤ ግን በደሉ አላቆም አለ፤ ማንም ሊደርስለት አለመቻሉ ይበልጥ ያሳዝናል፣ በእሱ ላይ ተከታታይ  የደረሰበት በደል የሕግ ያለህ የሚያሰኝ ነው፤ በቴዎድሮስ ካሣሁን ላይ በተቀነባበረ መንገድ የሚፈፀመው ማሰቃየት ማንንም ሰው የሚያሳስብ ነው፤ ምክንያቱ ምንድን ነው? በግልጽ የታወቀ ነገር የለም።

በቴዎድሮስ ላይ ከባድ ተንኮል ሲፈጸምበት የሰማሁት በመጀመሪያ ዛሬ በስደት ላይ ባለው « አዲስ ነገር» የሚባል ጋዜጣ ላይ ነበር፤ ጋዜጣው ቴዎድሮስ በሙያው ያገኘውን መልካም ስም በሰፊው ጥላሸት ቀብቶት ነበር፤ በጣም ሰፊ የሆነ ሀተታ በቴዎድሮስ ዘፈኖች ላይ በማቅረባቸው ምን ያህል አንገብጋቢ የአገር ጉዳይ አግኝተውበት ይሆን ብዬ አነበብሁት፣ ምንም ለአገር  የሚጠቅም ጉዳይ አላገኘሁበትም፤ በዘፈኖቹ ላይ በተደረገው ሂስም ከጋዜጠኞቹ መሀከል የሙዚቃ ሙያ ባለቤት እንዳለ ብጠይቅም ጋዜጣው ባለሙያ እንደሌለውና ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ ባለሙያ ማማከራቸውን ነገሩኝ፣  ስሙ  እንዲጠቀስ የማይፈልግ ባለሙያ፣ ባለሙያ አይባልም፣ እንኳን በሙያው በራሱም አይተማመንም ማለት ነው፤ በዚህ በራሱ በማይተማመን ሰው ምስክርነት ላይ በተመሰረተ ረጅም ነቀፌታ ቴዎድሮስን ደበደቡት፤

ሁለተኛው የቴዎድሮስ ጣጣ በመኪና ሰው ገጭቷል ተብሎ መከሰሱ ነው፤ በሌሊት፣ በጨለማ ነው፤ ቴዎድሮስ እንደሚለው  «እኔ ወደአገሬ የገባሁት ሰውዬው ሞተ በተባለበት ቀን ማግስት እንደሆነ ቪዛዬ ያረጋግጣል፣»  (ነጋድራስ መስከረም 30/2001 ዓ.ም. ) በኋላም ከዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል የተገኘው መረጃ ይህንኑ የሚያረጋግጥ እንደነበረ ተነግሮአል፤  በዚሁ በነጋድራስ ጋዜጣ ላይ የሚከተሉት መረጃዎች ተጠቅሰዋል ፦
ሙሉውን አንብብ-Read More

Ethiopia: Why Israeli delegation were Expelled from 23rd AU Summit?

Geez Bet | Monday, June 30, 2014
Addis Ababa (HAN) June 27, 2014. Regional Africa security and partnership update:  by. Ofer Petersburg, the opening ceremony for the 23rd African Union Summit in Malabo was to begin Thursday with a declaration of support for the three kidnapped Israeli teens by a number of participants, until bad blood brought tensions to a boil. Scheduled declaration of support from African nations scrapped; Arab League representatives demand ‘Israelis’ leave before joining summit.

“I have never seen such racism, such anti-Semitism. We were humiliated,” said several of the Jews in attendance, who had left Equatorial Guinea in a fury after changing their flights.
“It all began when one of the Arab delegates, from Egypt, approached us at dinner the night before the opening and asked what we were doing here, pointing at the men wearing kippahs,” said Israeli businesswoman Yardena Ovadia, who had organized the invitation of the Jewish delegation to the summit.
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 29, 2014

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ከግብፅ ፕሬዚዳንት ጋር በሰባት ነጥቦች ላይ ተግባቡ

Geez Bet | Sunday, June 29, 2014
በኢኳቶሪያል ጊኒ ዋና ከተማ በተካሄደው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ስብሰባ ላይ የተገናኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና የግብፅ ፕሬዚዳንት  አብዱልፈታህ አልሲሲ፣ በዓባይ ወንዝ አጠቃቃምና የታላቁ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ በሰባት ነጥቦች መግባባት ላይ ደረሱ፡፡

የግብፅ ሚዲያዎች መግባባቱን አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ሲሉ፣ አንዳንድ የኢትዮጵያ የውኃ ሀብት ባለሙያዎች ደግሞ የመግባቢያ ነጥብ ቁጥር አምስት ይዘት ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል የሚል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ሁለቱ መሪዎች በአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ተገናኝተው ባደረጉት የጎንዮሽ ውይይት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በፀጥታና በአካባቢያዊ ግንኙነቶች ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የሁለትዮሽ ኮሚሽን ለመመሥረት ተስማምተዋል፡፡
የዓባይ ወንዝ ለግብፃዊያን የመኖራቸው ወይም የህልውናቸው ጉዳይ መሆኑን፣ ለኢትዮጵያውያን ደግሞ የልማት ጥያቄ እንደሆነ መግባባታቸውን የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡
የዓባይ ውኃ አጠቃቀምን በተመለከተ ባደረጉት ውይይትም በሰባት ነጥቦች ላይ ከመግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 27, 2014

በሀልዎተ-እግዚአብሔር ዙሪያ በሻይ ቤት የተደረገ ሙግት

ZETOBIA | Friday, June 27, 2014
      (በካሣሁን ዓለሙ)


አንድ ቀን ፒያሣ በሚገኝ አንድ ኬክ ቤት ውስጥ የሃይማኖት መጽሐፍ እያነበብኩ ቁጭ ባልኩበት አንድ ዕድሜው በ20ዎቹ መጀመሪያ የሚገኝ ወጣት አጠገቤ መጥቶ በመቀመጥ ጨዋታ ጀመረ፡፡ የማነበውንም መጽሐፍ ‹እስቲ ልየው› ብሎኝ አሳየሁት፡፡ ከመጽሐፉ ጋር ተያይዞ ባነሳቸው ጥያቄዎችና ነቀፌታዎች የተነሳ የሚከተለውን ክርክር ተጨቃጭቀን ተለያየን፡፡
ልጁ ክርክሩን የጀመረውም “አሁን ይህንን መጽሐፍ ብለህ ታነባለህ?” በሚል ነበር፡፡
እኔም ተናድጄ “ለምን አላነበውም መጽሐፍ አይደለም?” ብዬ በጥያቄ መለስኩለት፡፡
“ማለቴ በዚህ መጽሐፍ ጊዜህን ከምታባክን ለምን የተሻለ እውቀት ያላቸውን መጻሕፍት አታነብም?”
“ምን ዓይነት መጻሕፍት ናቸው የተሻለ ዕውቀት ያላቸው?”
“ለምሳሌ የፍልስፍና መጻሕፍትን አታነብም? ሰዎች ለጥቅማቸው ሲሉ እግዚአብሔር ፣ ሰይጣን፣ ኃጢያት፣ ጽድቅ፣ ኩነኔ ምናምን እያሉ የጻፉትን ተረታተረት ከምትለቃቅም?” አለኝ እያጣጣለ፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 25, 2014

ምኒልክ እና አርሲ - (ወርቁ ፈረደ)

Geez Bet | Wednesday, June 25, 2014
ኢትዮጵያዊው ቢስማርክ ዳግማዊ ምኒልክ፣ አገር ለማስገበር ካደረጓቸው ዘመቻዎች ውስጥ ትልቅ ምከታ የገጠማቸው አርሲ ላይ ነው፡፡ ምኒልክ በአርሲዎች ክንድ ተከታታይ ሽንፈት ከቀመሱ በኋላ፣ በራስ ወልደ ገብርኤልና በራስ ዳርጌ እልክ አስጨራሽ ዘመቻ አማካኝነት፣ አሸንፈው አርሲን ወደ ግዛታቸው ቀላቀሉት፡: በጦርነቱ ከአስገባሪውና ከገባሪው ወገን አያሌ ወታደሮች አልቀዋል፡፡
ውጊያው የተካሄደው፣ነፍጥ በታጠቁ የንጉሱ ወታደሮችና ከጦርና ጋሻ ፈረስ ውጭ ምንም በሌላቸው የአርሲ ጎበዞች መካከል በመሆኑ፣ ከተከላካዩ ወገን ያለቀው በቁጥር እንደሚልቅ እሙን ነው፡፡ የአርሲ ጦርነት ከተካሄደ ከጥቂት አመታት በኋላ፣ ወደ ኦሮሞ ምድር የደረሰው ደ ሳልቪያክ የተባለ የፈረንሳይ ሀዋርያ ከአርሲዎች በሰበሰበው መረጃ ተመስርቶ እንደጻፈው፣ ራስ ወልደገብርኤል የአርሲዎችን አይበገሬነት ለመስበር ባንድ ቀን ብቻ የአራት መቶ አንጋፋዎችን ክንድ አስቆርጠዋል፡፡ይህ ጻሀፊ፣ ክንዳቸውን ካጡት ትልልቅ ሰዎች ጥቂቶቹን ባይኔ በብረቱ አይቻለሁ ብሏል፡፡
            ይህ የታሪክ ዘገባ በዘመናችን ፖለቲከኞች ሁለት ዓይነት ምላሽ እየተሰጠው ነው፡፡ የመጀመሪያው ምላሽ ክስተቱን ‹‹አይደረግም›› ብሎ መካድ ሲሆን፤ በተቃራኒ ወገን ያለው ደግሞ በማጋነንና በማራገብ ተጠምዷል፡፡ባለፈው ሳምንት ሀብታሙ አያሌው የተባለ ጸሀፊ በዚህች መጽሔት ላይ ሲጽፍ፣ የአርሲን የበደል ታሪክ፣ የቡርቃ ዝምታ ልቦለድ ውጤት እንደሆነ ሊያሳምነን ይፈልጋል፡፡ በኔ አስተያየት ይሄ አይነቱ ድርቅና ማንንም አይጠቅምም፡፡ አርሲ በስጦታ ወይም በስምምነት የተደባለቀ አገር አይደለም፡፡ የተገኘው በብዙ አገሮች እንደተደረገው፣ በጉልበትና በነውጥ ነው፡፡በወቅቱ ሰብአዊ ጥሰቶች በገባሪው ወገን ላይ መድረሳቸውን መካድ አስፈላጊ አይደለም፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

አንዲት ኢትየጵያዊት በጅዳ ቆንስል ግቢ ታንቃ ተገኘች

Geez Bet | Wednesday, June 25, 2014
በሳውዲ አረቢያ ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ግዜያዊ የስደተኞች መጠለያ ውስጥ እንዲት ኢትዮጵያዊት ታንቃ መገኘቷ የአካቢውን ማህበረሰብ ደረት ሲያስደቃ መዋሉን ቦታው ላይ የነበሩ የአይን እማኞች አረጋግጠዋል። ዛሬ በኢትዮጵያ ሰአት አቋ ጣጠር ከቀኑ 10
ሰአት ቆንስላው ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ታንቃ የተገኘቸው ወጣት በ 20 አመት የእድሜ ክልል ውስጥ የምትገኝ መሆኗን የሚናገሩ እማኞች በኮንተራት ለስራ መጥታ ከአሰሪዎቾ ባለመስማቷ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ግዜያዊ መጠለያ ኮንቴነር ውስጥ ለረዥም ወራት ስትሰቃይ የኖረች ሳትሆን እንደማትቀር ይናገራሉ ; ፡ በኢትዮጵያ ሰዓት አቋጣጠር ዛሬ ከቀኑ 10 አካባቢ እዚህ ቆንስላ ግቢ ውስጥ የታነቀቸውን ወጣት በአይናቸው ለማየት እድል ያገኙ እማኞች ወጣቷ እራሷን አንቃ ለመግደል ስትወራጭ አንገቷ ውስጥ የገባው ገመድ መስል ነገር ጉሮሮዋን ቆርጧ ወዲያው ሳይገድላት እንዳልቀረ ይገልጻሉ።

ይህ ዜና እስከ ተጠናከረበት ግዜ ድረስ የወጣቷ ሬሳ አለመንሳቱን የሚናገሩ ምንጮች በአካባቢው የፓስፖርተ እድሳት እና መስል ተዘማጅ ጉዳዩቹን ለማስፈጸም የቆንስላ ግቢውን አጨናነቀው እምባ ሲራጭ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከቆንስላው ጽ/ቤት እንዲወጡ መደረጋቸውን የአይን እማኞቹ አክለው ገልጸዋል ። ይህ በዚህ እንዳለ የሬሳ ጉዳይ የሚከታተለው እና የቀድሞ የኮሚኒቲ አመራር አቶ መሃመድ ሸህ ተፈቅዶለት ወደ ግቢው ሲገባ ያዩ ምንጮች ቦታው ላይ የሳውዲ ፖሊሶች እና ዲፕሎማቶች መገኘታቸውን
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 23, 2014

በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ወራሪው ማን ነው? ተወራሪዎቹስ?

Geez Bet | Monday, June 23, 2014
በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ታላቅ የሕዝብ ቅልቅል ተካሂዷል። ከእነዚህ ምክንያቶች መካከል፦ የአህመድ ግራኝ ወረራ፣ የኦሮሞ ወረራ፣ በዘመነ መሣፍንት የነበሩት የእርስ በእርስ ጦርነቶች፣ ፈፃሜ-ዘመነ
መሣፍንትን ያበሠሩት የማዕከላዊ መንግሥትን እንደገና የማዋቀር ጦርነቶች እንዲሁም ሁለቱ የኢጣሊያ ወረራዎች የሚጠቀሱ ናቸው። እነዚያ ጦርነቶች እና የእርስ በእርስ ግጭቶች ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የሕዝብ ክፍል ሕይዎት እንዳሣጡ አይካድም። ያንንም ተከትሎ ከኑሮ አስገዳጅነት እና በአገዛዝ ኃይሎች የበላይነት የያዘው አካል በሚፈጥረው የፖለቲካ አሠላለፍ መለዋወጥ ምክንያት የአንዱ ጎሣ ወይም ነገድ አባሎች በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመጥፋት ጉዳት ደርሶባቸዋል። በዚህ ረገድ ከኢትዮጵያ ዋና ዋና ነገዶች እና ጎሣዎች መካከል፦ በምዕራብ ኢትዮጵያ ነዋሪ የነበሩት የጋፋት ነገድ በኦሮሞ ወረራ ሙሉ በሙሉ እንዲጠፉ ሆነዋል ወይም ማንነታቸውን ተገድደው ለውጠው «ኦሮሞዎች» ወይም «ዐማራዎች» ወይም በሌላ ነገድ ስም ይጠራሉ፤ የሜያ ነገድ ተወላጆች ደግሞ በግራኝ አህመድ እና በኋላም ተከትሎ በመጣው በኦሮሞዎች ወረራ ምክንያት ቁጥራቸው በእጅጉ ተመናምኖ ዛሬ በዝዋይ ኃይቅ ውስጥ በሚገኙ ደሴቶች እና አካባቢው ብቻ ተወስነው ይገኛሉ። ጥንት በባሊ (ባሌ) እና ፈጠጋር (አርሲ) ተስፋፍተው ይኖሩ የነበሩት ሐዲያዎች እና ከንባታዎች በኦሮሞዎች ወረራ ተጨፍልቀው «ኦሮሞዎች» ሲባሉ ቀሪ ወገኖቻቸው በደቡብ ምዕራብ ሸዋ በአንድ ጠባብ አካባቢ በተጨናነቀ ሁኔታ እንዲኖሩ ተገድደዋል። ከዚህ በተጨማሪም፦ አርጎባዎች፣
ሙሉውን አንብብ-Read More

መኢአድ የአባሎች ግድያና እስራት መባባሱን ገለፀ

Geez Bet | Monday, June 23, 2014
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ በየቦታው በአባላቶቼ ላይ የሚደርሰው ግድያና እስራት ተባብሶ ቀጥሏል፤ ይህንንም አወግዛለሁ ሲል ለአዲስ አድማስ ገለፀ፡፡ በምስራቅ ጎጃም ዞን እነማይ ወረዳ ደንጎሊማ ቀበሌ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ላይ የፓርቲው የቀበሌ ተጠሪ የነበሩት አርሶ አደር ሞሳ አዳነ በታጣቂ ካድሬዎች ተደብድበው ህይወታቸው ማለፉን መኢአድ ገልጿል፡፡
በወረዳው የፓርቲው ምክትል ሰብሳቢና የዞኑ ወጣቶች ጉዳይ ተጠሪ መቶ አለቃ ደምመላሽ ጌትነት ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፣ ሟቹ አርሶ አደር ከዚህ ቀደም በመኢአድ አባልነታቸው የተነሳ ከእድርና ከቤተክርስቲያን እንዲገለሉ በመደረጋቸው፣ መገለሉ እንዲነሳላቸው ለወረዳው መስተዳደር አቤቱታ አቅርበው ነበር፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ከአሥር ወራት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ያጡ የፍቼ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሠልፍ ሊወጡ ነው

Geez Bet | Monday, June 23, 2014
-ካህናትና የነዋሪዎች ተወካዮች ዋና መሥሪያ ቤቱን ተማፀኑ:-
ላለፉት አሥር ወራት ከኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ኩራዝ ብርሃን ለመመለስ ተገደናል ያሉ በኦሮሚያ ክልል የፍቼ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች፣ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ ለከተማው አስተዳደር ጥያቄ ማቅረባቸውን አስታወቁ፡፡

ነዋሪዎቹ ሠልፍ እንደሚወጡ የከተማውን አስተዳደር መጠየቃቸውን የገለጹት፣ ነዋሪዎቹን ወክለውና የከተማውን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት አባቶችን ልብሰ ተክህኖ በመልበስና ሌሎች የሃይማኖት ተወካዮች እንደእምነታቸው ለብሰው፣ ፒያሳ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ተገኝተው ቅሬታቸውን ባሰሙበት ወቅት ነው፡፡
የፍቼ ከተማ ነዋሪዎች ላለፉት አሥር ወራት የኤሌክትሪክ ኃይል አጥተው መክረማቸውን የመሥሪያ ቤቱ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት እማኝ መሆኑን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ ከፍቼ እስከ አዲስ አበባ ከተማ ያሉትን ቢሮዎች ቢያዳርሱም፣ አንዱ ወደ ሌላኛው ቢሮ እንዲሄዱ ከመንገር ባለፈ የፈየዱላቸው እንደሌለ አስረድተዋል፡፡ ብሶታቸው እየባሰ በመምጣቱና ከመንግሥት አንድ ቁርጥ ያለ ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው በማመናቸው፣ ሁሉንም የከተማውን ነዋሪዎች በመወከል ከ25 የሚበልጡ ተወካዮች በዋናው መሥሪያ ቤት ተገኝተው ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ኦክስፎርድ፡ ኢትዮጵያ ከዓለም 2ኛዋ ድሃ አገር ናት

Geez Bet | Monday, June 23, 2014
ኢትዮጵያ ከ108 የዓለም ሃገራት በድህነት ከአፍሪካዊቷ ሃገር ኒጀር ቀጥላ ሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ  የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ጥናት ያመለከተ ሲሆን የኢኮኖሚ  ባለሙያዎች ሃገሪቷ ድሃ መሆኗ የሚስተባበል አይደለም ብለዋል፡፡
ሰሞኑን  ዩኒቨርሲቲው ይፋ ባደረገው የጥናት ውጤት፤ በኢትዮጵያ ከሚኖሩ ዜጎች 76 ሚሊዮን ያህሉ ድሆች ሲሆኑ በድሆች ብዛትም ከህንድ፣ ከቻይና፣ ከባንግላዴሽና ፓኪስታን ቀጥሎ ኢትዮጵያ  በ5ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች ብሏል፡፡
የድህነት መጠኑን በመቶኛ ስሌት ያስቀመጠው ጥናቱ፤ ኢትዮጵያ ከአጠቃላይ ህዝቧ 87.3 በመቶው ድሃ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 58.1 በመቶው ለኑሮው አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች ያልተሟሉለት ምስኪን ተመፅዋች ዜጋ ነው ብሏል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የአገራትን የድህነት ደረጃ የለካው የትምህርት፣ የጤናና የኑሮ ሁኔታዎችን መሰረት ያደረጉ አስር መስፈርቶችን  በመጠቀም ሲሆን፣ በአገሪቱ በገጠር ከሚኖረው ህዝብ 96.3 በመቶው፣ ከከተማ ነዋሪው ደግሞ 46.4 በመቶው  በድህነት አረንቋ ውስጥ እንደሚኖር በሪፖርቱ  ተመልክቷል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Egyptian anchorwoman suspended after live row with Ethiopia envoy

Geez Bet | Monday, June 23, 2014
An Egyptian broadcaster has been suspended for arguing with Ethiopia's ambassador to Cairo during a live TV phone-in about Addis Ababa's ongoing Nile dam project.
On Wednesday, Rania Badawy, a talk show host on the privately-owned Tahrir satellite channel, got into a heated argument with Ethiopian envoy Mahmoud Dardir over the Grand Renaissance Dam, a multi-billion hydroelectric dam that has been a source of contention between the two countries for over a year.
Near the end of the six-minute-long call, Badawy asked the envoy if Addis Ababa insisted on pressing forward with the dam's construction in its current form and capacity, which Egypt fears will harm its share of the Nile's water.
The ambassador replied: "You do not understand about dams and are talking in a bumptious tone."
Badawy then angrily told the ambassador he had "crossed his limits" and that he should not "characterise [her] talk or speak to [her] about arrogance". She then thanked him and abruptly ended the call, as his voice trailed off in an attempt to reply.
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 20, 2014

ሰበር ዜና- ምዕራብ ወለጋ ከጊምቢ እና ቄሌም (እንፍሌ ወረዳ አሽ ቀበሌ) በሺህ የሚቆጠር የአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ተፈናቀሉ።

Geez Bet | Friday, June 20, 2014
በሺህ የሚቆጠር የአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ከምዕራብ ወለጋ ጊምቢ እና ቄሌም በኃይል አካባቢውን እንዲለቁ ከመደረጉ በላይ  ድብደባ እና ግድያ እንደተፈፀመባቸው ቪኦኤ የአማርኛው አገልግሎት ሰኔ 12/2006 ዓም ምሽት ባስተላለፈው ዘገባ ገለፀ።
ዘገባው የተፈናቃዮችን ምስክርነት እንዳስደመጠው ድብደባው እና ግድያው በከተማው ሕዝብ እና ፖሊስ የታገዘ መሆኑን እና ህይወታቸውን ያተረፉት በኮርኒስ እና ጫካ በመደበቅ መሆኑን ሲገልጡ፣አንድ ምስክርነታቸውን ለቪኦኤ የሰጡ ተፈናቃይ አክለው እንደገለፁት ከጊምቢ ከተማ ብቻ ከሶስት ሺህ በላይ የአማርኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን መፈናቀላቸውን ተናግረዋል።ሌላው ምስክርነት ሰጪ ደግሞ ቁጥሩን ከስምንት ሺህ ሕዝብ በላይ አድርሶታል።
አምስት ልጆች የነበራቸው መሆናቸውን የተናገሩት ሌላ ተፈናቃይ የነበራቸው መደብር መዘረፉን እና ካለምንም ሀብት መቅረታቸውን፣ጉዳዩን አቤት ለማለት ወደ ባለስልጣናት ቢሄዱም ሰሚ ማጣታቸውን አስታውቀዋል።
የቪኦኤ ጋዜጠኛ ጉዳዩን አስመልክቶ ቀደም ብሎ የአካባቢው የፀጥታ ጉዳይ ኃላፊ የተባሉ እሳቸው ግን የኦሕዴድ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ነኝ ያሉ አቶ አወቀ የተባሉ የክልሉ ባለሥልጣን ስለጉዳዩ ሲናገሩ ''ያባረረ የለም' ሲሉ ተደምጠዋል።
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 19, 2014

South Sudan’s Kiir writes protest letter to Ethiopian PM

Geez Bet | Thursday, June 19, 2014
June 17, 2014 (JUBA) – South Sudanese president Salva Kiir has written to the East African regional bloc (IGAD) demanding an apology over remarks allegedly made by one of its officials.
The letter, foreign affairs minister Benjamin Marial said, was delivered by a government minister to Ethiopia’s prime minister, Hailemariam Desalegn, who is the current IGAD chairperson.
IGAD’s executive secretary Mahboub Maalim allegedly described president Kiir and rebel leader Riek Machar as “stupid” for pursuing military means instead of peace talks the ongoing conflict.
Marial said statements attributed to Mahboub was “unfortunate", given the regional body’s mediation role.
“The government, specially our president, has sent an envoy to with a letter to prime minister of Ethipia with regards to the unfortunate statement which was said by executive secretary of the IGAD in the press,” Marial told reporters in Juba Tuesday.
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 18, 2014

Ethiopia ranks second poorest country in the world - Oxford University Study

Geez Bet | Wednesday, June 18, 2014
 According to The Global Multidimensional Poverty Index (MPI), published by Oxford University, Ethiopia ranks the second poorest country in the world just ahead of Niger. The study is based on analysis of acute
poverty in 108 developing countries around the world. Despite making progress at reducing the percentage of destitute people, Ethiopia is still home to more than 76 million poor people, the fifth largest number in the world after India, China, Bangladesh and Pakistan. India has the world's largest number of poor people at more than 647 million.
87.3% of Ethiopians are classified as MPI poor, while 58.1% are considered destitute. A person is identified as multidimensionally poor (or 'MPI
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 16, 2014

ማን ይንገርልን – ማን ይመስክርልን (ጸጋዬ ገብረ መድኅን አርአያ)

Geez Bet | Monday, June 16, 2014
እንደ ልጄ የምቆጥረውና ከበኩር ልጄ ከዩሐንስ ጋር ያደገው ሳምሶን በሕክምና ኮሌጅ ይማር በነበረበት ዘመን በምሽቱ ሰዓት ላይ የ‹‹ፈገግታ ጊዜ›› በምንለው ግማሽ ሰዓት ያጫውተን ነበር፡፡ አዎን ሕይወት ውጥርጥር ባለበትና ጭንቀት ከቀበሌ ከሚወረወር ቀስት፣ ጭንቀት ከየካድሬውና ከየፖለቲካው ኅቡዕ ድርጅት ከሚወረወር ሌላ ቀስት፣ ጭንቀት፣ ከመስሪያ ቤት ጭንቀት፣ ከበላይ አካል ጭንቀት፣ ከበታች አካል ጭንቀት፣ ጭንቀት —- አንድ የድሮ ማስታወቂያ ሚኒስትር እንዳሉት ከላይ ከመሳፍንቱና ከመኳንንቱ በሚለቀቅብህ እሳት፣ ከታች ከሕዝቡና ከሠራተኛው ከሚነድድብህ እሳት የገና ዳቦ ትሆናለህ፡፡ ስለዚህ ‹‹በታይም አውት›› (ፋታ ልበለው) መልክ ከሳሚዬ ጋር የማደርገው የግማሽ ሰዓት ውይይት (ጨዋታ) ለእኔ “ማሳጅ” ነበር፡፡
 መታሻ!

እንደ ወትሮው የዛሬው ወጋችን በክፍል ውስጥ ስለነበረው አጋጣሚ ነበር፡፡ በዚያው ዕለት በሕክምናው ኮሌጁ የመጀመሪያው ሰዓታት (ሦስት) አስተማሪው ዶክተር አሥራት ወልደየስ ነበሩ፡፡ “ዛሬ የማስተምራችሁ ስለ ጦር ሜዳ አነስተኛ የቀድዶ ሕክምና ነው” ይላሉ፡፡ አከታትለውም የጦር ሜዳውን “ሰገሌ እንበለው” ይላሉ፡፡ ይቀጥላሉ፡፡ ተፋላሚዎች በወሎው ጦር በኩል “ንጉሥ
ሙሉውን አንብብ-Read More

ወጣቶቹና- ቅዳሜ፣ አንዷን ቅዳሜ በፍርድ ቤት (ጽዮን ግርማ)

Geez Bet | Monday, June 16, 2014
ለአብዛኛው ወጣት አዲስ አበባ ላይ ‹‹ቅዳሜ›› ትርጉም አላት፡፡ የሣምንቱን የሥራ ቀናት በየፈርጁ ያሳለፈው ኹሉም ወጣት ‹‹ቅዳሜ››ን ደግሞ እንደየ ምድቡ ይውልባታል፡፡ እንደሰማኹት ከኾነ ለዞን ዘጠኝ አባላትና ጓደኞቻቸውም ቅዳሜ ልዩ ቀን ናት፡፡ ለወጣቶቹ አብሮነት የጡመራ መድረኩ ቢያግዛቸውም ከዛ በላይ ግን ጓደኝነታቸው ቤተሰባዊነትን ፈጥሮላቸው አብዛኛውን ቅዳሜ እንደየ ቅርበታቸው አብረው ያሳልፋሉ፡፡
አብረው እስረኛ ይጠይቃሉ፣የታመመን ያጽናናሉ፣በጋራ ምሳ ይቋደሳሉ፣የተለየ ዝግጅት ካለም አብረው ይሳተፋሉ፡፡ ከዚህ የተረፈ ጊዜ ካላቸው ደግሞ ፈጣንንና ነጻ የገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት በሚገኝበት ሆቴል ገብተው ዓለም በምን ኹኔታ ላይ እንዳለች ለመከታተል ይሞክራሉ፡፡ አገሪቷ ውስጥ ባለው ከፍተኛ የኢንተርኔት ኮኔክሽን ችግር ምክንያት አብዛኛው ጋዜጠኛና ጥቂት ወጣቶች የእነዚህ ትልልቅ ሆቴሎች ገመድ አልባ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ኢስተር ራዳ ከአመቱ 50 የዓለማችን ተጽዕኖ ፈጣሪ አይሁዳውያን አንዷ ሆነች

Geez Bet | Monday, June 16, 2014
የእስራኤል ፕሬዚዳንት፣ ጠ/ሚንስትር፣ የገንዘብ ሚ/ር እና የኢኮኖሚ ሚ/ር በዝርዝሩ ውስጥ ተካተዋል:- 
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ታዋቂ ድምጻዊት ኢስተር ራዳ፣ ‘ዘ ጀሩሳሌም ፖስት’ ጋዜጣ የአመቱ የዓለማችን ተጽዕኖ ፈጣሪ አይሁዳውያን ብሎ ከመረጣቸው 50 ታዋቂ ግለሰቦች መካከል አንዷ ሆነች፡፡ 

በሶል፣ በአር ኤንድ ቢ እና በፋንክ ስልቶች የተቃኙና የኢትዮ-ጃዝ ቃና ያላቸው ሙዚቃዎችን የምትጫወተውና “የእስራኤል የሶል ሙዚቃ ንግስት” በመባል የምትጠራዋ ኢስተር ራዳ፣ በእስራኤል ብቻም ሳይሆን በመላ አለም በርካታ አድናቂዎችን ማፍራት የቻለች ድምጻዊት መሆኗን ‘ዘ ጀሩሳሌም ፖስት’ ባለፈው ሰኞ ይፋ ባደረገው መረጃ መስክሮላታል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

መኢአድና አንድነት በአንድ ወር ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ይዋሀዳሉ

Geez Bet | Monday, June 16, 2014
 በሁለቱም ወገን የተመረጠው ውህደት አመቻች ኮሚቴ ሰኞ ስራ ይጀምራል:- 
         የአራት አመት የድርድርና የምክክር ጊዜ የፈጀው የመላው ኢትዮጵያ ድርጅት (መኢአድ) እና የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ቅድመ ውህደት ባለፈው እሁድ የተፈረመ ሲሆን ሁለቱ ፓርቲዎች በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ እንደሚዋሀዱ የፓርቲዎቹ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ አንድነት ፓርቲ ነገ ብሄራዊ ምክር ቤቱን ለአስቸኳይ ስብሰባ የጠራ ሲሆን የስብሰባው ዓላማም የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴን ለመምረጥ እንደሆነ ገልጿል፡፡
ኮሚቴው በብሄራዊ ም/ቤቱ እንደሚሰየም የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ተናግረዋል፡፡ የመኢአድ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለአዲስ አድማስ እንዳብራሩት፤ የመኢአድ ስራ አስፈፃሚ አምስት አባላት ያሉት የውህደት አመቻች ኮሚቴ መርጦ ለአንድነት በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን አባላቱ አቶ ወርቁ ከበደ፣ አቶ ተስፋሁን አለምነህ፣ አቶ ሲራክ አጥናፍ፣ አቶ
ሙሉውን አንብብ-Read More

የዶ/ር ኢ/ር ሳሙኤል ዘሚካኤል የትምህርት ማስረጃዎች ሐሰተኛ ናቸው ተባለ

Geez Bet | Monday, June 16, 2014
በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በሰጡት ቃለ-ምልልስ ሲቪል መሀንዲስ እንደሆኑና ከአውስትራሊያና ከሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ መመረቃቸውን ሲገልፁ የቆዩት የዶ/ር ኢንጂነር ሳሙኤል ዘሚካኤል የትምህርት ማስረጃዎች ሀሰተኛ እንደሆኑ ሬድዮ ፋና ትላንት ዘገበ፡፡
ኢ/ር ሳሙኤል በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ቃለ-ምልልስ ከሰጡ በኋላ እንግዳ አድርገዋቸው እንደነበር የገለፁት የ“አዲስ ጣዕም” አዘጋጆች፤ ኢ/ር ሳሙኤል በ1996 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሲቪል ምህንድስና ድግሪያቸውን ሲቀበሉ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ እንደነበሩ፣ ከአውስትራሊያና ከሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ መመረቃቸውንና ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የክብር የተባባሪ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እንዳገኙ መናገራቸውን አስታውሰዋል፡፡ አዘጋጆቹ የመረጃዎቹን ትክክለኛነት ሲያጣሩ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ1991 ጀምሮ ሳሙኤል ዘሚካኤል በሚባል ስም የተመዘገበና የተመረቀ ለማወቅ እንደሌለ ገልፀዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jun 12, 2014

በምስራቅ ጎጃም አርሶ አደሮች በፖለቲካ አመለካከታቸው የተነሳ ማዳበሪያ እየተከለከሉ ነው ተባለ

Geez Bet | Thursday, June 12, 2014
(ነገረ ኢትዮጵያ) በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶነሴ ወረዳ አርሶ አደሮች በፖለቲካ አመለካከታቸው ልዩነት ምክንያት ማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየተከለከሉ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አስታወቁ፡፡ መንግስት
ለአርሶ አደሮች በህብረት ስራ ማህበራት የግብርና ግብዓትና ግብይት በኩል የሚያቀርብ ሲሆን ይህም ማዳበሪያ የሚሸጠው የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት ላይ ነው፡፡ ሆኖም ሁሉም አርሶ አደሮች የማዳበሪያና የምርጥ ዘር አቅርቦት የማያገኙና ይህም ከአመለካከት ጋር በተያያዘ መሆኑን ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡
አርሶ አደሮች ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እንዳያገኙ ከተደረጉባቸው ምክንያቶች የመጀመሪያ ተብሎ የተቀመጠው ለመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን መዋጮ ያላዋጡት ሲሆን፣ 1997 ምርጫ ተቃዋሚ የነበሩ እንዲሁም ገዥው ፓርቲ በአርሶ አደሩ ላይ ባደራጃቸው 15 አደረጃጀት ጥናት መሰረት ‹‹ተቃዋሚ ናቸው›› የተባሉ አቅርቦቱን እንዳያገኙ ተደርጓል ተብሏል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More