Time in Ethiopia:

Feb 26, 2014

<< የፀረ ግብረ ሰዶማዊ ሕጐችን ማውጣት የመንግሥታት ሥራ አይደለም>> ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014

በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ የሰፈረው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል!

-መንግሥት አካውንታቸው ተጠልፏል እያለ ነው::
የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በትዊተር ማኅበራዊ ገጻቸው ላይ፣ ‹‹በተወዳጇ አፍሪካዬ ውስጥ ጥላቻና መገለል ቦታ የላቸውም፡፡
የአለባበስ ሥርዓት ወይም የፀረ ግብረ ሰዶማዊ ሕጐችን ማውጣት የመንግሥታት ሥራ አይደለም፤›› በሚል የወጣው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ መንግሥት ግን የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መጠለፉን ገልጾ፣ ይህ መልዕክት የሚኒስትሯንም ሆነ የመንግሥትን አቋም አይወክልም ሲል አስተባብሏል፡፡ 

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በኡጋንዳ የፀደቀውን ፀረ ግብረ ሰዶማዊያን ሕግ በመቃወም በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ የተጻፈው ይህ መልዕክት፣ በዓለም ዙሪያ ባሉ የግብረሰዶማዊ መብቶች አቀንቃኞች አድናቆት ተችሮታል፡፡ ሆኖም ግን የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ዓብይ ኤፍሬም፣ ‹‹መልዕክቱ በማይታወቁ ሰዎች የተጻፈ ሲሆን፣ የእሳቸውንም ሆነ የመንግሥትን አቋም የማይገልጽ ነው፤›› ብለዋል፡፡ 
አቶ ዓብይ አክለው፣ ‹‹ሚኒስትሯ ይህን የማኅበረሰብ ሚዲያ የሚጠቀሙት ሕዝቡ በቀጥታ ሊያገኛቸው የሚገቡ መልዕክቶችን ለማስተላለፍ አዋጭ ሚዲያ በመሆኑ ነው፤›› ብለዋል፡፡ የትዊተር ገጻቸውን የሚያንቀሳቅሱት ራሳቸው ወይዘሮ ዘነቡ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ዓብይ፣ በገጻቸው ላይ በጠላፊዎች በተላለፈው መልዕክት ሚኒስትሯ ማዘናቸውን አስረድተዋል፡፡ 
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መጠለፉን አረጋግጠው፣ ‹‹የሚኒስትሯን አካውንት ጠልፈው በመግባት የእሳቸውንና የመንግሥትን አቋም የማይገልጽ
ሙሉውን አንብብ-Read More

ዩጋንዳና ግብረ ሰዶማዊነትን የሚቃወው ህጓ

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014
በዩጋንዳ ትናንት ጀምሮ ግብረ ሰዶማዊነት የሚቃወም ህግ ተደንግጓል ። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የዩጋንዳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግብረ ሰዶማዊነትን በመቃወም ባለፈው ታህሳስ ያሳለፈውን ህግ ትናንት በፊርማቸው አፅደድቀዋል ። ህጉ የፀደቀው በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና ግብረሰዶማዊነትን በሚቃወሙ ወገኖች መካከል ለዓመታት ከተካሄደ ትግል በኋላ ነው ። በአዲሱ ህግ የሰዶማዊነት ተግባር በእድሜ ልክ እሥራት ያስቀጣል ። አዲሱ ህግ ከመፅደቁ በፊት ብዙ ጊዜ ወስዷል ።
እጎአ በ2009 ነበር ግብረ ሰዶማዊነትን የሚቃወም ረቂቅ ህግ ለዩጋንዳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ። የያኔው ረቂቅ ህግ በተደጋጋሚ የግብረ ሰዶም ተግባር ሲፈፅም በተገኘ ሰው ላይ እስከ ሞት ቅጣት የሚደርስ ብይን እንዲተላለፍ የሚደነግግ ነበር ። ይህም በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ ። በመጨረሻም መቀመጫውን ካምፓላ ያደረገው የሃገሪቱ ፓርላማ ባለፈው ታህሳስ ቅጣቱን ወደ እድሜ ልክ እስራት ዝቅ ያደረገውን ህግ አሳለፈ ። ዩጋንዳ በብሪታኒያ
ሙሉውን አንብብ-Read More

በኑሮ መማረሩን ተናግሯል የተባለው የጥበቃ አባል ራሱን አጠፋ

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014
በቦሌ ዋናው መንገድ ከሚሊኒየም አዳራሸ ማዶ በሚገኘው የሕብረት ባንክ አክሲዮን ማኅበር ቅርንጫፍ በጥበቃ ሥራ ላይ የተሰማራው ወጣት፣ ‹‹ኑሮ መሮኛል›› በማለት እየተናገረ ለጥበቃ በያዘው ጠመንጃ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ ራሱን አጠፋ፡፡
ወጣቱ የጥበቃ ሠራተኛ በሱፈቃድ በጋሻው በኪሱ ውስጥ ከተገኙት የተለያዩ መታወቂያዎች መረዳት እንደተቻለው፣ አጋር የጥበቃ ሠራተኞች ማሠልጠኛ ተቋም ተቀጣሪ ነው፡፡ በተጨማሪም የኮሌጅ ተማሪ መሆኑን በሚገልጸው መታወቂያ ላይ እንደሠፈረው ከሆነ፣ በ1982 ዓ.ም. የተወለደና የ24 ዓመት ወጣት ነው፡፡ በምን ምክንያት ከፖሊስ ባልደረባነት እንደለቀቀ ባይታወቅም፣ የ13ኛ ኮርስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባል እንደነበር በቅርብ ከሚያውቁት ወዳጆቹ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በባንኩ አሠራር አንድ የጥበቃ አባል 24 ሰዓት ሠርቶ 24 ሰዓታት የሚያርፍ በመሆኑ፣ ሟች በሱፈቃድም የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት አዳሪ ጓደኛውን ከቀየረ በኋላ፣ ባንኩን ለመጠበቅ የቻለው ለ24 ሰዓታት ሳይሆን ለሰባት ሰዓታት ብቻ ነው፡፡ ወጣቱ ‹‹ኑሮ መሮኛል›› በማለት እያማረረ እያለ በመሀል የያዘውን ጠመንጃ ቃታ በመሳብ አንድ ጊዜ ወደ ላይ ሲተኩስ፣ አብረውት የነበሩ ሴት ፈታሽና ሌሎች የባንኩ ተጠቃሚዎች በመደናገጥ ወደ ውስጥና ወደ ውጭ ሽሽት ይጀምራሉ፡፡ ሁለተኛውን ጥይት በመተኮስ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ በኩል በፍጥነት መራመድ መቀጠሉን በሥፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡ 
ሦስተኛውን ጥይት ወደ ላይ ከተኮሰ በኋላ አራተኛውን አንገቱ
ሙሉውን አንብብ-Read More

ግብፅ በህዳሴው ግድብ ላይ የጀመረችውን ዘመቻ ዓለም አቀፍ ገጽታ ልታላብሰው ነው

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014
-ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከነካቢኔያቸው ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ
የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ የጀመረውን ዘመቻ ዓለም አቀፍ ገጽታ ለማላበስ አዲስ እንቅስቃሴ ሊጀምር ነው፡፡
ከወደ ግብፅ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የግብፅ የውኃና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ይህንን አዲስ እንቅስቃሴ ያስተባብራሉ፡፡ 
ከዚህ ቀደም ግድቡን በተመለከተ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ፀጥታው ምክር ቤት አቤቱታ ለማቅረብ የተጀመረው እንቅስቃሴ ተገትቶ፣ አዲሱ ዘመቻ ፊቱን ወደ ጣሊያንና ኖርዌይ አዙሯል፡፡ ከዚያም ወደተለያዩ አገሮች ይቀጥላል፡፡ 
ባለፈው ሳምንት የውኃ ሚኒስትሩ መሐመድ አብዱል ሙታሊብና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነቢል ፋህሚ ወደ ጣሊያን ጉዞ አድርገዋል፡፡ የግብፅ መንግሥት ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ ዋነኛ ሸሪክና የግድቡ ግንባታ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ ባሉዋት ጣሊያን የተደረገው ጉብኝት ስኬታማ ነበር ብለዋል፡፡ 
   የጣሊያኑ ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ኩባንያ የግድቡን ጥናትና ግንባታ የሚያካሂድ በመሆኑ፣ ጣሊያን የግብፆች የአዲሱ ዘመቻ ዓላማ መሆኗ እየተነገረ ነው፡፡ የውኃ ሚኒስትሩ ሙታሊብ ለግብፅ ሚዲያዎች እንደገለጹት፣
ሙሉውን አንብብ-Read More

የሱዳን ወዳጅነት ከጉርብትናም በላይ?

Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014
ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ በእያንዳንዱ የሕወሓት የልደት በዓል ማለትም የካቲት 11 በዋነኝነት ከሚከበርበት የትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ተገኝተው በሚያደርጉት ንግግር በዓሉን ሁሌም ድምቀት ይሰጡት ነበር፡፡
ሥልጣን ላይ ያለው ኢሕአዴግ ዋነኛ መሥራች የሆነውን ሕወሓት የረጅም ጊዜ ጠንካራ ሊቀመንበሩን ያጣው ባለፈው ዓመት በዓሉን ከማክበሩ ስድስት ወራት በፊት ነበር፡፡
አቶ መለስ ለመጀመርያ ጊዜ ያልተገኙበት 38ኛው በዓል ግን እሳቸውን በመዘከር በሐዘን ድባብ ነበር ያለፈው፡፡ ተተኪያቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝም በወቅቱ በበዓሉ ላይ ቢገኙም፣ በአቶ መለስ መሪነት እዚህ ደርሷል ያሉት ሥርዓት ከፍተኛውን መስዋዕትነት ከፍሎበታል ካሉት ከትግራይ ሕዝብ ጋር እጅና ጓንት በመሆን እንደሚሠሩ፣ ‹‹የማፅናኛ›› ንግግር አድርገው ነበር የተመለሱት፡፡ 
ዘንድሮ የተከበረው 39ኛው የሕወሓት በዓል ግን ባለፈው ዓመት በሐዘን ድባብ ያለፈውን በዓል ያካካሰ በሚመስል ሁኔታ እጅግ ደማቅ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ላለፉት 22 ዓመታት ሥልጣን ላይ የቆየው ኢሕአዴግ ዋነኛ አካል የሆነው ሕወሓት፣ በሚቀጥለው አርባኛ የልደት ዓመቱ በበለጠ በደመቀ ሁኔታ ያከብራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የዘንድሮው ግን ከተገመተው በላይ ደማቅ ሆኖ ተከብሯል፡፡ 
የሕወሓት በዓል እጅግ እንዲደምቅ ምክንያት የሆነው ባለፉት ሁለት ዓመታት የተለየ የሠራው ነገር ኖሮ አይመስልም፡፡ እንዲያውም ድርጅቱ ጠንካራ መሪውን በሞት ካጣ በኋላ መረጋጋት ተስኖት በውስጥ መከፋፈልና እርስ በርስ በመወነጃጀል ማሳለፉ ይነገራል፡፡ የድርጅቱ ሌሎች አንጋፋ መሪዎችም ያላግባብ ከአመራር መሸኘቱ ከፍተኛ ትችት ያስተናገደበት ዓመት ነበር፡፡ በሌሎች ዓመታት እንደተለመደው
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 24, 2014

ዝምተኛው የአውሮፕላን ጠላፊ

Geez Bet | Monday, February 24, 2014
ቅዳሜ የካቲት 8 ቀን 2006 ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደንበኞች ቀንን በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ባከበረበት ወቅት፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም በመቶዎች ለሚቆጠሩ የአየር መንገዱ ደንበኞች አየር መንገዱ ስለደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዝርዝር ማብራሪያ ሲሰጡ ነበር፡፡
የአገር ባህል ልብስ ለብሰው ፈገግታ ሳይለያቸው የአየር መንገዱን ስኬት ሲያስረዱ ‹‹ዋካ ዋካ›› በሚለው በሻኪራ ተወዳጅ ዜማ ታጅበው ነበር፡፡ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪና የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት አብዱሰላም አቡበከር፣ ታዋቂ ባለሀብቶችና ዲፕሎማቶች በተገኙበት በዚህ ደማቅ ሥነ ሥርዓት ላይ አቶ ተወልደ የአየር መንገዱን ስኬት በኩራት አስረድተዋል፡፡

በእርግጥም አየር መንገዱ ባለፉት አምስት ዓመታት በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ይገኛል፡፡ የዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ቁጥር 79 አድርሷል፡፡ የአውሮፕላኖቹን ቁጥር ደግሞ ወደ 63 አሳድጓል፡፡ እጅግ ዘመናዊ የሚባለውን ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን እጁ በማስገባት ከአፍሪካ አንደኛ፣ ከዓለም ሦስተኛው አየር መንገድ ለመሆን በቅቷል፡፡ ገቢውን በሰባት እጥፍ በማሳደግ 2.1 ቢሊዮን ዶላር አድርሷል፡፡
የዚያን ዕለት በአየር መንገዱ ስኬት ሲፍነከነኩ የነበሩትን አቶ ተወልደን ለተመለከታቸው ሰው፣ ከአንድ ቀን በኋላ አስደንጋጭ ዜና ይነገራቸዋል ብሎ በፍፁም ሊያስብ አይችልም ነበር፡፡ የሆነው ግን እንደዚያ ነው፡፡
እሑድ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. ሌሊት ለሰኞ አጥቢያ 202 መንገደኞችንና የአውሮፕላኑን ሠራተኞች አሳፍሮ ከአዲስ አበባ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 23, 2014

የኢቴቪ ዋና ዳይሬክተር ታስረው እንዲቀርቡ ታዘዘ

Geez Bet | Sunday, February 23, 2014
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት እየታየ በሚገኘው 28 ተከሳሾች ላይ ለቀረበ የአቃቤ ህግ የቪዲዮ ማስረጃ አስተርጓሚ እንዲመድብ የታዘዘው የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት፤ የፍ/ቤቱን ትዕዛዝ ተግባራዊ ባለማድረጉ ዋና ዳይሬክተሩ ፍ/ቤት ታስረው እንዲቀርቡ ታዘዘ፡፡
በእነ አማን አሠፋ መዝገብ በሚገኙ የሽብር ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ የሰው ምስክሮችንና በሺዎች የሚቆጠሩ የሰነድ ማስረጃዎችን ለፍ/ቤቱ አቅርቦ ያጠናቀቀ ሲሆን በአረብኛና በኦሮሚኛ ቋንቋዎች ለቀረቡት የቪድዮ ማስረጃዎች ኢሬቴድ አስተርጓሚ እንዲመድብ ከፍ/ቤቱ የተላለፈውን ትዕዛዝ ተግባራዊ አላደረገም ተብሏል፡፡ በዚህም ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ብርሃኑ ኪዳነማርያም ታስረው ፍ/ቤት እንዲቀርቡ ታዟል፡፡
ቀደም ሲል እነዚህን የሽብር ተጠርጣሪዎች አስመልክቶ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን “ጅሃዳዊ ሃረካት” የሚል ዶክመንተሪ ፊልም ተዘጋጅቶ መሰራጨቱ የሚታወስ ሲሆን አቃቤ ህግም በክስ ማመልከቻው፣ ተጠርጣሪዎች የአልቃይዳ ህዋስ ሆነው በአለማቀፍ የሽብር መዋቅር ውስጥ ተሳታፊ እንደነበሩ ማመልከቱ ይታወሳል፡፡
Source: Addis Admass
 
ሙሉውን አንብብ-Read More

በተጠለፈው አውሮፕላን ውስጥ የነበረው ኢትዮጵያዊ እማኝነት

Geez Bet | Sunday, February 23, 2014
“የተሳፋሪው ፍላጎት የሆነ መሬት ላይ ማረፍ ብቻ  ነበር”
በሃዋሳ ከተማ በተለምዶ ኬሮ ሰፈር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተወልዶ ያደገው ወጣት ምህረቱ ገብሬ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በቀድሞው ሀዋሳ ኮምቦኒ የመጀመርያ ደረጃ ት/ቤት ነው የተከታተለው። የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያና የመሰናዶ ትምህርቱንም በቅዱስ ዳንኤል ኮምቦኒ የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ት/ቤት አጠናቋል። ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2001 ዓ.ም በሲቪል ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪውን ካገኘ በኋላም፤ እስከ 2004 ዓ.ም ድረስ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በመምህርነት አገልግሏል፡፡ በመቀጠልም ነጻ የትምህርት ዕድል በማግኘት፣ ወደ ጣሊያን አምርቶ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በመከታተል ላይ ይገኛል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 20, 2014

መሬትና ዉሃ ቅርምት በኢትዮጵያ

Geez Bet | Thursday, February 20, 2014
ኢትዮጵያ ዉስጥ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቡን እየጎዳ እንደሚገኝ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተሟጋች ሂዉማን ራይትስ ዎች አመለከተ። ድርጅቱ ይህን አመልክቶ ባወጣዉ ዘገባ በዚህ ምክንያትም ኢትዮጵያና ኬንያ ዉስጥ 500,000 አርብቶ አደሮች ለችግር መጋለጣቸዉን ገልጿል። 
ሂዉማን ራይትስ ዎች፤ ኢትዮጵያ፤ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቦችን ጎዳ በሚል ዛሬ ባወጣዉ ዘገባ፤ አዳዲስ ከሳተላይት የተገኙ ምስሎች በታችኛዉ ኦሞ ሸለቆ አካባቢ ነባር ማኅበረሰቦች ይጠቀሙበት የነበረዉን መሬት ለስኳር ልማት በስፋት መመንጠሩን ማሳየታቸዉን አመልክቷል። ላለፉት አምስት ወራትም 7,000 የሚሆኑ የቦዲ ጎሳ አባላት ጋ በቂ ምክክር ሳይደረግ ተግባሩ መከናወኑን ዘርዝሯል። የድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳይ ምክትል ዳይሬክተር ሌስሊ ሌፍኮ፤ ድርጅታቸዉ በUNESCO በዓለም ቅርስነት
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 19, 2014

Sudan FM criticises Egypt over Ethiopian dam dispute

Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014
February 18, 2014 (KHARTOUM) –Sudanese foreign minister Ali Karti has criticised Egypt for its handling of a dispute involving the construction of a massive dam project in Ethiopia, which it has vehemently opposed over concerns it could disrupt water flows from the Nile river.
Karti said Egypt was further inflaming the situation by making critical comments in the media, adding that Sudan would continue its efforts to bridge the gap between the two countries.
“The position of Sudan is clear and we have already called on Egyptian officials to take advantage of the central role that Sudan could play regarding the crisis, but the arrogance
ሙሉውን አንብብ-Read More

የጠላፊው ረዳት አብራሪ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል

Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014
-  መንግሥት ተላልፎ እንዲሰጠው ይፈልጋል:
ባለፈው እሑድ ሌሊት 6፡30 ሰዓት ከአዲስ አበባ ወደ ሮም መብረር የጀመረውን የበረራ ቁጥሩ ‹‹ET 702›› የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን የጠለፈው ረዳት አብራሪው ኃይለመድኅን አበራ ተገኝ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
ጠለፋውን ፈጸመ የተባለው ረዳት አብራሪ ቤተሰቦች መሆናቸውን የሚናገሩ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኃይለመድኅን ላይ ያልተለመዱ ባህሪዎችን መመልከታቸውን ይናገራሉ፡፡
ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ደግሞ ግለሰቡ በተለያዩ ጊዜያት የዲስፒሊን ችግሮች ቢኖሩበትም፣ ብቃት ያለው አብራሪ እንደነበረ ገልጸዋል፡፡
ጉዳዩን በተመለከተ ባለፈው ሰኞ ከቀትር በኋላ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚነስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ግለሰቡ ጠለፋውን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳው እንቆቅልሽ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
‹‹አንድ ሰው በጠለፋ ወንጀል ከተሰማራ ቢያንስ 20 ዓመት ነው የሚፈረድበት፡፡ ከ20 ዓመት በኋላ ምን እንደሚያትርፍ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም፤›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ ምን ዓይነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች እንደገፉት ለማወቅ ምርመራ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡
ረዳት አብራሪ ኃይለመድኅን የ31 ዓመት ወጣት ሲሆን፣ በአየር መንገዱ ለአምስት ዓመታት ያገለገለ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሬድዋን፣ በግለሰቡ የግል ሕይወት ዙሪያ በምርመራ የተደረሰበት መረጃ በአሁኑ ወቅት እንደሌለ ጠቁመዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ሦስት የግብፅ የፖለቲካ ፓርቲዎች ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲቋረጥ ለዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረቡ

Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014
የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ ሲካሄድ የቆየው የሦስትዮሽ ውይይት ከተቋረጠ ከሳምንታት በኋላ፣ ሰሞኑን ሦስት የግብፅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የግድቡ ግንባታ እንዲቋረጥ ለዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረቡ፡፡
‘ዲሞክራቲክ ፒፕል ፓርቲ’፣ ‘ኢጂፕቲያን ዓረብ ሶሻሊስት ፓርቲ’ እና ‘ሶሻል ጀስቲስ ፓርቲ’ የተባሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ዘ ሄግ ለሚገኘው ዓለም አቀፍ የፍትሕ ፍርድ ቤት፣ ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ እንድታቆም የሚጠይቅ ማመልከቻ አስገብተዋል፡፡ 
ግብፅ በየዓመቱ 55 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውኃ ከዓባይ ተፋሰስ እንደምትጠብቅ የተናገሩት የዲሞክራቲክ ፒፕል ፓርቲ ሊቀመንበር ፉአድ ሃፌዝ፣ ባለፈው መስከረም ወር የወንዙ ፍሰት በ20 ቢሊዮን ኪዩቡክ ሜትር ቅናሽ ማሳየቱን አመልክተዋል፡፡
የፍርድ ቤቱን አንቀጽ 40 እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን አንቀጽ 96 በመጥቀስ አቤቱታ ማቅረብ መብታቸው መሆኑን የተናገሩት የፓርቲዎቹ መሪዎች፣ ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ምንም ዓይነት ግድብ እንዳትገነባ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
በመስኖ ውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የወሰንና የወሰን ተሻጋሪ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 17, 2014

Co-pilot hijacks plane to Geneva, seeks asylum

Geez Bet | Monday, February 17, 2014
GENEVA (AP) -- An Ethiopian Airlines co-pilot locked his colleague out of the cockpit, hijacked a Rome-bound plane and landed Monday in Geneva, all in an attempt to seek asylum in Switzerland, officials said.
The Boeing 767-300 plane with 202 passengers and crew had taken off from the Ethiopian capital of Addis Ababa and landed in the Swiss city at about 6 a.m. (0500 GMT). Officials said no one on the flight was injured and the hijacker was taken into custody after surrendering to police.
It wasn't immediately clear why the co-pilot, an Ethiopian man born in 1983 whose name wasn't released, wanted asylum. However, Ethiopian Airlines is owned by Ethiopia's government, which has faced persistent
ሙሉውን አንብብ-Read More

አሳሳቢው የመምህራን ፍልሰት

Geez Bet | Monday, February 17, 2014
ቦሌ መሰናዶ ትምህርት ቤት ውስጥ መምህራንና ተማሪዎች በመማር ማስተማሩ ሒደት ለመምከር ተሰባስበዋል፡፡
የ‹‹ትምህርት ለሁሉም›› 2013/14 ሪፖርት ይፋ መሆንን ተከትሉ ውይይቱን ለማድረግ ለተወከሉት ተማሪዎች ሴራሊዮናዊው አወያይ ቼርኖር ባህ ‹‹መምህር መሆን የሚፈልግ አለ?›› ሲል ጥያቄውን ሰነዘረ››፡፡ ከደቂቃዎች ዝምታ በኋላ አንድ ተማሪ ‹‹እኔ መሆን እፈልጋለሁ፡፡ አንድ ጥያቄ ለመምህራኑ እንድጠይቅ ግን ፍቀድልኝ›› አለች፡፡ ሚስተር ባህ መድረኩን ሰጣት፡፡ ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣ ከማላዊና ከፓኪስታን ለተወከሉት መምህራን ‹‹ከእናንተ ውስጥ ልጁ መምህር እንዲሆን የሚፈልግ አለ?›› ስትል ጠየቀች፡፡ አንድም መምህር አዎ ሲል አልተደመጠም፡፡ 

ቤተሰብ በልጁ ላይ ከሚፈጥረው የ‹‹መምህር አትሆንም›› ተፅዕኖ በተቃራኒ ልጁ መምህር እንዲሆንለት የሚፈልግ እንዲሁም በፍላጐት ወደ ዘርፉ የሚቀላቀሉ አሉ፡፡ ሆኖም ዛሬ ዓለም እያስተናገደች ያለችው ከፍተኛ የመምህራን እጥረትና ፍልሰትን ነው፡፡ በየትምህርት
ሙሉውን አንብብ-Read More

‹‹ከኢትዮጵያ ጋር ከመደራደር ይልቅ ሌሎች አማራጮችን መውሰድ እንፈልጋለን›› የግብፅ የውኃ ሚኒስትር

Geez Bet | Monday, February 17, 2014
-ግብፅ  ከኢትዮጵያ ጀርባ ቱርክ አለች ማለት ጀመረች
ባለፈው ሰኞ በአዲስ አበባ ለውይይት መጥተው ስብሰባው ተቋርጦ ወደ አገራቸው የተመለሱት የግብፅ የውኃና መስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ካይሮ ሲደርሱ በሰጡት መግለጫ፣ ከኢትዮጵያ ጋር መደራደር እንደበቃቸው ከገለጹ በኋላ ‹‹ሌሎች አማራጮችን መውሰድ እንፈልጋለን፤›› ብለዋል፡፡

ሚኒስትሩ በደፈናው ሌሎች አማራጮችን ከማለት ውጪ ማብራሪያ አልሰጡም፡፡ ይሁን እንጂ ንግግራቸውን በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ያነበቡ ኢትዮጵያውያን ንግግሩን ፀብ አጫሪነት ነው ብለው፣ ‹‹ኢትዮጵያውያን ግድቡን እንገነባለን፣ ግብፆች ያላቸው ሌላ አማራጭ ምን እንደሆነ እናያለን፤›› በማለት በቁጣ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
‹‹የኢትዮጵያ የመንግሥት ባለሥልጣናት ግብፅን የመጉዳት ፍላጎት የለንም እያሉ ነው፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 15, 2014

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሠራተኞች በአስተዳደራዊ ችግር ተማረናል አሉ

Geez Bet | Saturday, February 15, 2014
“የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች አሉባልታ ነው” - ዩኒቨርስቲው

በባህርዳር ዩኒቨርስቲ አስተዳደራዊ ችግር መማረራቸውን የተናገሩት የዩኒቨርስቲው ሠራተኞች፤በየጊዜው  መምህራን ሥራቸውን እየለቀቁ እንደሚወጡ ገለፁ፡፡ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ በበኩላቸው፤ የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች አሉባልታ እንጂ በዩኒቨርስቲው ውስጥ አስተዳደራዊ ችግር እንደሌለ  ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
በዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የሚመደብለት፣ ከ45 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሚያስተምርና ከአምስት ሺህ በላይ ሰራተኞች የሚያስተዳድረው ዩኒቨርስቲው፤ ከአመራርና አስተዳደር ሙያ ጋር የተገናኘ የትምህርት ዝግጅት በሌላቸው አመራሮች እየተመራ፣ ለከፍተኛ አስተዳደራዊ ችግር መጋለጡን ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልፀዋል፡፡
 አንድ የዩኒቨርስቲው ሠራተኛ በሰጠው አስተያየት፤ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ በፊዚክስ፣ምክትሉ ዶ/ር ፍሬው አሞኜ በእንስሳት ህክምና፣ሌላው ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር እያዩ  በባዮሎጂ የተመረቁ መሆናቸውን በመጠቆም፣ አንዳቸውም በአስተዳደር ወይም በአመራር ሙያ አለመመረቃቸውን አስረድቷል፡፡ “አመራሩ ለምን በተፈጥሮ ሳይንስ ምሁራን በሞኖፖል እንደተያዘ አልገባኝም” ብሏል፡፡ የፕሬዚዳንትና የምክትል ፕሬዚዳንቶቹ እርስ በእርስ አለመግባባትና በየስብሰባው መዘላለፍ ሌላው የአስተዳደሩን ችግር ያባባሰ ጉዳይ መሆኑን የሚገልፁት ቅሬታ አቅራቢዎች፤ የአመራሮቹ ውዝግብ በተቀረው ሰራተኛ ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩን አልሸሸጉም፡፡
ዩኒቨርስቲው ከ159 ሚሊዮን ብር በላይ አውጥቶ ከከተማው ማዘጋጃ ቤት ለመምህራን ኮንዶሚኒየም ቤቶች ቢገዛም እስካሁን  ለመምህራኑ አላስረከበም ሲሉ የሚወቅሱት ሠራተኞቹ ፤ህንፃዎቹ ያለ አገልግሎት ቆመው እየተሰነጣጠቁና ለመፀዳጃነት እየዋሉ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ዩኒቨርስቲው እስካሁን ወደ 20 ሚሊዮን ብር መክሰሩንና ህንፃዎቹን ለማደስ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚጠብቀው ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርስቲው አመራር፣ የመምህራርንንም ሆነ የሌሎች ሠራተኞችን ቅሬታ ለመስማትና መፍትሄ ለማበጀት ዝግጁ አይደለም የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በዚህም የተነሳ በተለይ ወጣቶችና ትዳር ያልያዙ መምህራን በአስተዳደራዊ ችግር እየተማረሩ በየጊዜው ሥራቸውን እየለቀቁ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው ሁለት ምክትል ዲኖችም ከመማረራቸው የተነሳ የአገልግሎት ክፍያ ሳያገኙ ሥራቸውን ጥለው እንደወጡ ገልፀዋል፡፡
የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ በበኩላቸው፤ ሠራተኞች የሚለቁት የተሻለ ደሞዝ ሲያገኙ እንጂ በአስተዳደራዊ ችግር እንዳልሆነ ይናገራሉ፡፡ አስተዳደራዊ ችግር እንዳለ የሚያወሩት የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች እንደሆኑም ገልፀዋል - ፕሬዚዳንቱ፡፡ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ በአገር ውስጥ ካሉት ምርጥ ዩኒቨርስቲዎች ከሦስተኛ እስከ አምስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት ዶ/ር ባይሌ፤  የተለያዩ መሥሪያ ቤቶች በቀጥታ ከዩኒቨርስቲው በርካታ ምሩቃንን እንደሚቀጥሩ ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው አመራር የትምህርት ዝግጅት፣ ከአስተዳደር ሙያ  ጋር ስለማይገናኝ ዘርፈ ብዙ አስተዳደራዊ ችግሮች እየተፈጠሩ ነው በሚል የተነሱ ቅሬታዎችንም ፕሬዚዳንቱ አይቀበሉትም። “ማንኛውም ሰው የመጀመርያ ድግሪውን በየትኛውም ዘርፍ ሊሰራ ይችላል፤ ለምሳሌ የአገሪቱ ጠ/ሚኒስትር የመጀመርያ ድግሪ ከአመራር ጋር የተገናኘ አይደለም” ያሉት ዶ/ር ባይሌ፤ አንድ ሰው ተመራማሪ መሆኑ ከአመራርነት አያግደውም ሲሉ ተሟግተዋል፡፡ እኔ የፊዚክስ ሰው ስለሆንኩ መምራት አልችልም ማለት አይደለም ያሉት ዶ/ሩ፤ ይሄ የሚያሳየው የቅሬታ አቅራቢዎቹን አላዋቂነት ብቻ ነው ብለዋል፡፡ የፕሬዚዳንቶቹን አለመግባባትና መዘላለፍ በተመለከተ ሲያስረዱም ፤ በሃሳብ አለመግባባትና የሃሳብ ልዩነትን እንደተራ ጠብ ማየት የግንዛቤ ችግር ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ዋናው ለአላማ መሥራት እንጂ የሰዎች ግንኙነት መሆን የለበትም  ብለዋል፡፡  
ከከተማው ማዘጋጃ ቤት ለመምህራን የተገዙትን ቤቶች በተመለከተ ሲመልሱም “ዩኒቨርስቲው ቤት ለመግዛት ብር ከፈለ እንጂ ቤት አይገነባም” ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ መረጃ ሰጪዎቹ ያለ እውቀት ወሬ ይዘው የሚሮጡ በመሆናቸው ነው እንጂ ችግሩ የተከሰተው በቤቶች ልማት አቅም ማነስ እንደሆነ ተረጋግጦ፣ ዩኒቨርስቲው የቤቶቹን የማጠናቀቂያ  ሥራ ለመሥራት ውሳኔ ላይ ደርሷል ብለዋል፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት ዩኒቨርስቲው የገዛውን ይሄንኑ ኮንዶሚኒየም ለመምህራኑ ሳያስረክብ በመቅረቱ  ዩኒቨርስቲው ለ20 ሚሊዮን ብር ኪሳራ መዳረጉን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
Source: addis Admass
 
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 13, 2014

‹‹ከኢትዮጵያ ጋር መታረቅ ስለሚባለው ባልሰማውና ባላስበው እመርጣለሁ›› ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ

Geez Bet | Thursday, February 13, 2014
የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የሥልጣን ዘመናቸውን ከጨረሱ በኋላ፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥታትን ማስታረቅ እንደሚፈልጉ የመንግሥት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሆነው ኢቴቪ በይፋ ገልጸው መስመር የያዘላቸው መሆኑንም አሳውቀው ነበር፡፡

በቅርቡ ከኤርትራ ቴሌቪዥን ጋር ሰፊ ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግን ምንም ዓይነት የዕርቅ ፍላጐት እንደሌላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በፕሮፓጋንዳ ብልጫ እየተጠቀመበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያን በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄ የሰጧቸው ምላሾች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡  
‹‹የሕዝብ ግንኙነት ብልጫ ለማግኘት ነው››
ሁለት የኤርትራ የመንግሥት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች አንዳንድ የአገር ውስጥና የአካባቢ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ጥያቄዎችን ለፕሬዚዳንት ኢሳያስ አንስተውላቸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያና በኤርትራ ግንኙነት ላይ የሰጡት አስተያየት አነጋጋሪ ነው፡፡ 
በመግለጫው ከተገኙ የመንግሥት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ እንዲህ ብሎ ፕሬዚዳንቱን ይጠይቃቸዋል፤ ‹‹ኤርትራና ኢትዮጵያን ለማስታረቅ አንዳንድ ሙከራዎች እየተደረጉ እንደሆነ በሚዲያዎች እየተነገረ ነው፡፡ ይኼ የሚወራው ነገር እውነት ነው ወይ?›› ይላቸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ለጥያቄው መልስ መስጠት ሲጀምሩ ፊታቸውን ጨለም አድርገዋል፡፡ የሆነ ከውስጥ የሚሰማ የቁጣ ስሜት እንዳለ
ሙሉውን አንብብ-Read More

የግብፅ ሚኒስትር የግድቡ ግንባታ እንዲቆም በመጠየቃቸው ውይይቱ ተቋረጠ

Geez Bet | Thursday, February 13, 2014
የግብፅ የውኃና መስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ በጠየቁት መሠረት ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ ቢገቡም፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲቆም በመጠየቃቸው ውይይቱ በሰዓታት ውስጥ ተቋረጠ፡፡

የግብፅ ሚኒስትር ከኢትዮጵያ አቻቸው አቶ አለማየሁ ተገኑና ከባልደረቦቻቸው፣ እንዲሁም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተወከሉ ባለሙያዎች ጋር ባለፈው ሰኞ መገናኘታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ 
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና ተያያዥ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ከጋዜጠኞች ጋር ለመወያየት ባዘጋጀው መድረክ ላይ የተገኙት አቶ አለማየሁ ተገኑ፣ የግብፅ አቻቸው ሁለት አጀንዳዎችን ይዘው መቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡ 
የግብፅ ሚኒስትር በስልክ ደውለው ወደ አዲስ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 10, 2014

የአንድነት ፓርቲ አመራር አቶ አሥራት ጣሴ ታሰሩ

Geez Bet | Monday, February 10, 2014
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የምክር ቤት አባል አቶ አሥራት ጣሴ ፍርድ ቤት በመድፈር ወንጀል ተከሰው ጥፋተኛ በመባላቸው፣ ጥር 30 ቀን 2006 ዓ.ም. በፖሊስ ጣቢያ ታሰሩ፡፡
አቶ አሥራት ለእስር የበቁበትን ፍርድ ቤት የመድፈር ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት፣ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ቅጽ 7 ቁጥር 198 የጥር ወር 2006 ዓ.ም. ዕትም ላይ በጻፉት ጽሑፍ ምክንያት ነው፡፡
አቶ አሥራት በመጽሔቱ ላይ ባሰፈሩት ‹‹…..አሁን ደግሞ ከሰሞኑ ‘አኬልዳማ’ ድራማ በድጋሚ በተከታታይ እየቀረበ ነው፡፡ ይህ እየሆነ ያለው አንድነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅትን በስም ማጥፋት ወንጀል በፍርድ ቤት ከሶ ገና ውጤት ባልተገኘበት
ሙሉውን አንብብ-Read More

የግብፅ እጅ መንሻ?

Geez Bet | Monday, February 10, 2014
በተጠናቀቀው ሳምንት የግብፅ ወጣት የዲፕሎማሲ ሠልጣኞች ቡድን በአዲስ አበባ የአንድ ሳምንት ቆይታ አድርጓል፡፡ ሪፖርተርን ጨምሮ የተወሰነ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞችም ጥሪ ተደርጐላቸው ከግብፅ ልዑካን ቡድን ጋር ለመነጋገርና ለመወያየት ተጋብዘዋል፡፡ 
በኢትዮጵያ የግብፅ አምባሳደር መሐመድ እድሪስ ስለ ቡድኑ መምጣት፣ ዓላማና ግብ እንዲሁም የቡድኑ አባላት ማንን እንዳነጋገሩ፣ የት የት እንደሄዱ ገልጸው፣ በየዓመቱ የግብፅ መንግሥት ሠልጣኝ ዲፕሎማቶቹን ወደ ኢትዮጵያና ሌሎች አፍሪካ አገሮች ልምድ እንዲቀስሙ እንዲህ ዓይነት ጉዞ እንደሚያዘጋጅላቸውና ይህም እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዲፕሎማሲያዊ ጉዞው ብቻ እንደ አንድ ልማድ ተደርጐ እየተወሰደ መሆኑን በኤምባሲው ለተገኙ የአገር ውስጥ ጋዜጠኞች ገለጻ አድርገዋል፡፡ 

የግብፅ አምባሳደር መሐመድ እድሪስ፣ ‹‹ሠልጣኞቹ በወሬ ከሚሰሙትና በቃል ከሚያወሩት እዚህ በአካል መጥተው ኢትዮጵያን መመልከታቸው እጅግ አስደስቷቸዋል፤ እናም ራሳቸው ሠልጣኞቹ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 5, 2014

ጉራማይሌ ፖለቲካ! (ተመስገን ደሳለኝ)

Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014
በምንወዳት ኢትዮጵያችን ከኑሮ እስከ ሮሮ፤ ከማሕበራዊ እስከ ፖለቲካ፤ ከኢኮኖሚ እስከ ትምህርት ፖሊሲ፤ ከመንፈሳዊ እስከ ዓለማዊ… ያሉ ጉዳዮች ጉራማይሌነት ከቀን ወደ ቀን እየጎላ ነው፡፡ በዚህ ፅሁፍም ጥቂት ያህል ማሳያዎችን በአዲስ መስመር እንመለከታለን፡፡
ጎንደር እና ጥምቀት
የሁሉም መነሻና መድረሻ ዓላማ መንፈሳዊ ይሁን እንጂ እንደ መስቀል፣ ጥምቀትና ሬቻ… ያሉ አንዳንድ በዓላት ከመንፈሳዊነታቸው በተጨማሪ የባሕል መገለጫ እስከመሆን ደርሰዋል፡፡ ከዚህ የተነሳም በዓላቶቹ በሚከበሩባቸው ቦታዎች የሚገኘው ስፍር ቁጥር የሌለው ሕዝብ፣ ሰማያዊውን ፅድቅ ብቻ ሳይሆን፣ በባህላዊው አከባበርም በእጅጉ ስለሚማርክ ጭምር ነው፡፡
የሆነው ሆኖ በወዳጆቼ ጋባዥነት የዛሬ አስራ አምስት ቀን በጎንደር ከተማ በተከበረው የጥምቀት በዓል ላይ ተገኝቼ ነበር፤ በወቅቱም የታዘብኩት ጉዳይ ከሺህ ዓመታት በፊት የተፈፀመ አንድ ክስተትን እንዳስታውስ
ሙሉውን አንብብ-Read More

ግብፅ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ጀመረች

Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014
-የግብፅ የልዑካን ቡድን በህዳሴው ግድብ ላይ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር ሊነጋገር ነው
የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በተመለከተ ሱዳን ለኢትዮጵያ የሰጠችውን ድጋፍ ለማጨናገፍ፣ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ መጀመርዋን ዘገባዎች አመለከቱ፡፡
የተለያዩ የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ሰሞኑን እንደዘገቡት፣ የግብፅ መንግሥት የተለያዩ የመንግሥት አመራሮችና ፖለቲከኞች ከሱዳን መንግሥት አቻዎቻቸው ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጀምረዋል፡፡

ለአብነት ከተጠቀሱት መካከል የግብፅ አል ዋፍድ ፓርቲ ሊቀመንበር ሳይድ አል ባዳዊ በካይሮ ከሱዳን አምባሳደር ከማል ሐሰን ዓሊ ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበር የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በዋነኝነት መክረዋል፡፡ በሁለቱ አገሮች ድንበር የጦር መሣሪያ ዝውውር ለማስቆም የተነጋገሩት ሁለቱ ባለሥልጣናት፣ ኢትዮጵያ
ሙሉውን አንብብ-Read More

የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ተማሪዎች ተጋጩ

Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014
በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ የኢንቫይሮመንታል ኢንጂነሪንግ ተማሪዎች ‹‹ኢንቫይሮመንትን በሚመለከት የምንማረው ትምህርት ስለሌለ ካሪኩለሙ ተቀይሮ ኃይድሮሊክ ኢንጂነሪንግ በሚል ይቀየርልን›› በማለት ከጥር 23 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የፖሊስ ሠራዊት ጋር መጋጨታቸውን፣ በሥፍራው የተገኙ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ 

ዩኒቨርሲቲው ፈንድ ስለሚያገኝበት ብቻ ኢንቫይሮንመንታል ኢንጂነሪንግ በሚል ስያሜ የማይማሩትን ትምህርት እንደተማሩ በማስመሰል ዲግሪ የሚሰጣቸው ከሆነ፣ በማይታወቅና ምንም ጥቅም በሌለው የትምህርት መስክ ከመቀመጥ ባለፈ ሌላ ጥቅም እንደማያገኙበት በመግለጽ፣ ካሪኩለሙ እንዲቀየር አጥብቀው መጠየቃቸውን ሪፖርተር ያጋገራቸው አንዳንድ ተማሪዎች አስረድተዋል፡፡ 
ሙሉውን አንብብ-Read More

የእግር ኳሱን አንኳር ችግር መንካት የተሳነው ግምገማ

Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014
ክስተቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጥሩም በመጥፎም እያነጋገረ ሰንብቷል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት አንዳንዶች ‹‹በአጋጣሚ›› አንዳንዶች ደግሞ ‹‹በጥረት›› በሚሉት መንገድ ወደ አፍሪካ ዋንጫ፣
እንዲያም ሲል ለዓለም ዋንጫ ማጣርያ ከአሥር የአፍሪካ ምርጦች አንዱ ሆኖ የመጣው የዋሊያዎቹ ቡድን፣ እንደ አመጣጡ መጓዝ ተስኖት የተሰናበተ የቻን የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ትዝብት ውስጥ ጥሎታል፡፡

አንድም ጐል ሳያስቆጥር በሁሉም ግጥሚያዎች ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ መሆኑ ብዙ አስነቅፎታል፡፡ ከሕዝቡ የተሰነዘረበት ትችት የበረታ መሆኑን ተከትሎ ተጨዋቾቹ፣ አሰልጣኙና ሌሎችም በቡድኑ ውስጥ ኃላፊነት ያላቸው አካላት ቅሬታቸውን ሲያሰሙ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Feb 4, 2014

የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ከአገር ኮበለሉ

Geez Bet | Tuesday, February 04, 2014
የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩትና በአሁኑ ሰዓት የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት የተከበሩ አቶ ኡመድ ኡባንግ፤ ከአገር መኮብለላቸውን ምንጮቻችን ገለፁ፡፡ አቶ ኡመድ ኡባንግ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከሃገር መውጣታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለሱ ለሚቀርቧቸው ሰዎች መናገራቸውን አመልክተዋል።
የሚኒስትር ዴኤታውን መኮብለል በተመለከተ የጠየቅናቸው የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም፤ አቶ ኡመድ በስራ ገበታቸው ላይ እንደሌሉ ማረጋገጣቸውን
ሙሉውን አንብብ-Read More