Time in Ethiopia:

Sep 30, 2013

ቃለመጠይቅ - ከተስፋዬ ገብረአብ ጋር

Geez Bet | Monday, September 30, 2013
"ለአማርኛ ስነፅሁፍ ቅርብ ነኝ ለማለት አልችልም። የሚታተሙ መጻሕፍትን እንደልቤ ለማግኘት ስለምቸገር ስለታተሙ መጻሕፍት በልበ ሙሉነት አስተያየት ለመስጠት እቸገራለሁ። በጥቅሉ ግን የአማርኛ ስነፅሁፍ አደጋ ላይ የወደቀ ሆኖ ይሰማኛል። አማርኛ በአዲሳባና በአማራ ክልል ቋንቋነት ብቻ ተወስኖ እንዲቀር ብዙ ተሰርቶበታል። ይህ ሁኔታ የአማርኛ ስነፅሁፍን ክፉኛ ጎድቶታል። አማርኛ ቋንቋ ጠላት ስለበዛበት ስነፅሁፉም ባለቤት አጥቶአል። ይህ አሳዛኝ እውነት ነው።" ተስፋዬ ገብረአብ ከላይፍ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለምልልስ
(ይህ ቃለመጠይቅ አዲስ አበባ ላይ በየ15 ቀኑ ከሚታተመው "ላይፍ" መጽሔት ጋር የተደረገ ሲሆን፤ ቃለመጠይቁ የተካሄደው ከመጽሔቱ ጋዜጠኛ ጋር በጽሑፍ ነው።)
ላይፍ፦ አዲሱ "የስደተኛው ማስታወሻ" መጽሐፍህ ከ"የደራሲው ማስታወሻ" እና ከ"የጋዜጠኛው ማስታወሻ" በምን ይለያል?
ተስፋዬ፦ "የስደተኛው ማስታወሻ" ከቀዳሚዎቹ ማስታወሻዎች የቀጠለ ነው። በዚህ ቅፅ በተመሳሳይ ገጠመኞቼን ነው ያሰፈርኩት።
ሙሉውን አንብብ-Read More

አወይ ሶሪያ - የኢትዮጵያ ጠላት

Geez Bet | Monday, September 30, 2013
ሰሎሞን ተሰማ ጂ.
የሶሪያ ጉዳይ ከዕለት ወደ ዕለት እየከፋ መጥቷል። በስልጣን ላይ ያለው ጎሳ "የአላዊት ጎሳ" ይባላል። አላዊቶችና በደዊኖች በሽፍትነትና በባህር ላይ ውንብድና ስማቸው የገነኑ ናቸው። በደዊኖች፣ ሶሪያን ለዘመናት ያህል ሲፈልጧትና ሲቆርጧት ኖረዋል። እንደነሱ ዘረኛ፣ እንደበደዊኖች ጠባብ፣ አክራሪና ቁመኛ ታይቶም-ተሰምቶም አይታወቅም። አላዊቶችም ቢሆኑ "አልሸሹም ዞር አሉ" ናቸው።

እነዚህ ወገኖች፣ የሶሪያን ሀገረ-መንግሥት (State apparatus) ከተቆጣጠሩበት ዘመን ጀምሮ ለኢትዮጵያ በጎ ተመኝተውላት አያውቁም። ይባስ ብሎ ደግሞ፣ ከ1950ዎቹ መጀመሪያ ወዲህ እጅግ በከፋ መልኩ የኢትዮጵያን ጥቅምና ሉዓላዊነት በሚፈታተን መልኩ በግትርነት ቆመው ነበር። በጣም በተጋነነና በመረረ ኹናቴ መንቀሳቀስ የጀመሩት ግን ከ1953ዓ/ም ወዲህ ነው። በዚህ
ሙሉውን አንብብ-Read More

ከአዲስ አበባ አዳማ ፈጣን መንገድ ለሚገናኘው የቀለበት መንገድ ቻይና 4.3 ቢሊዮን ብር ፈቀደች

Geez Bet | Monday, September 30, 2013
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ለሆነው ከአዲስ አበባ አዳማ የፍጥነት መንገድ ጋር ለሚያገናኘው የአዲስ አበባን ውጫዊ ቀለበት መንገድ ለመገንባት የሚያስፈልገውን 4.3 ቢሊዮን ብር ብድር፣ የቻይናው ኢምፖርት ኤክስፖርት (ኤግዚም) ባንክ ፈቀደ፡፡
በስምንት ቢሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኘውና በአሁኑ ወቅት ግንባታው 85 በመቶ የተጠናቀቀው በዓይነቱ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የፍጥነት መንገድ፣ በአዲስ አበባና በአዳማ መካከል ያለውን ርቀት ወደ 80 ኪሎ ሜትር የሚያሳጥር ነው፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ በዘንድሮው በጀት ዓመት የሚጠናቀቅ ቢሆንም፣ በአዲስ አበባ መግቢያ ላይ ተቀባይና ወደ መሀል ከተማ ሊያስገቡ የሚችሉ ተጨማሪ መንገዶች ካልተገነቡ፣ የፍጥነት መንገዱ እንዲሰጥ የሚፈለገውን ፈጣን ትራንስፖርት እንደሚያስተጓጉለው የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ተገንዝቦታል፡፡ 
ሙሉውን አንብብ-Read More

የአፍሪካ ኢኮኖሚ ሪፖርት ኢትጵያን ከፈጣን አገሮች ተርታ አላሰለፈም

Geez Bet | Monday, September 30, 2013
-የአፍሪካን ወቅታዊ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ ኩነቶች ዘንግቷል በሚል ተተቸ
የአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ምልከታን በመንተራስ በየዓመቱ ይፋ የሚደረገው ሪፖርት (አፍሪካን ኢኮኖሚክ አውትሉክ)፣ እ.ኤ.አ. በ2013 የነበረውንና በ2014 ይኖራል ብሎ የተነበየው የኢኮኖሚ መስተጋብር ይፋ ሲደረግ፣ አሥር ፈጣን አፍሪካ ኢኮኖሚዎች ካላቸው ውስጥ ኢትዮጵያ አለመካተቷ ስህተት መሆኑን ኃላፊዎቹ አመኑ፡፡
የአፍሪካ ልማት ባንክ ከሌሎች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀውን ሪፖርት ዘንድሮ ይዞ ብቅ ያለው፣ በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት ከሚያስመዘግቡ አሥር አገሮች መካከል ኢትዮጵያን ዘንግቶ ነው፡፡ ይህ የሆነው ግን ሪፖርቱ ከተዘጋጀ አንድ ዓመት በኋላ ይፋ በመደረጉ ነው ተብሏል፡፡ የቅርብ ጊዜ መረጃዎችን ለማካተት ሳይቻለው መቅረቱ ስህተት እንደሆነ የገለጹት የባንኩ የኢትዮጵያ ተወካይ ላሚን ባሮው፣ ምንም እንኳ ኢትዮጵያ በሪፖርቱ ከአፍሪካ ግንባር ቀደም ፈጣን አገሮች ውስጥ ስሟ ባይጠቀስም ዕድገቷ አይካድም ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የዘንድሮው ሪፖርት በአፍሪካ እየተካሄዱ ያሉ የፖለቲካ ለውጦችን በአግባቡ አላሳየም ሲሉ ከተቹ ምሁራን መካከል፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው ዶ/ር
ሙሉውን አንብብ-Read More

Sep 23, 2013

ከሰማይ ወረደ ለተባለው መስቀል የሳይንስ ምርመራ አይፈቀድም ተባለ

Geez Bet | Monday, September 23, 2013
ለህዝብ የሚታየው ፓትሪያርኩ በተገኙበት ነው:: በየእለቱ ከ3ሺህ ሰው በላይ ቦታውን እየጎበኘ ነው
በአቃቂ ቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን ከሰማይ ወረደ የተባለው መስቀል ፓትርያርኩ በተገኙበት ለህዝብ እንዲታይ መግቢያ መንገድ እስኪሰራ ድረስ የተራዘመ ሲሆን፣ በመስቀሉ ላይ የሳይንስ ምርመራ እንደማይፈቀድ ተገለፀ፡፡ ከሶስት ሳምንት በፊት በፍንዳታ ድምፅና በብርሃናማ ቀስተደመና ከሰማይ ወረደ የተባለው መስቀል፣ በሚቀጥለው ሳምንት መስከረም 19 ቀን ለህዝብ ይታያል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፣ ፓትርያርኩ የሚገኙበት ስነስርዓት ለማዘጋጀት ጊዜው እንደተራዘመ
ሙሉውን አንብብ-Read More

ለፕሬዚዳንት ግርማ በወር በ530 ሺሕ ብር ቤት ለመከራየት የተፈረመው ውል ፈረሰ

Geez Bet | Monday, September 23, 2013
የፕሬዚዳንትነት ቆይታቸውን በማጠናቀቅ ላለፉት 12 ዓመታት የቆዩበትን ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ለአዲሱ ፕሬዚዳንት እንደሚያስረክቡ ለሚጠበቁት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ መኖሪያ እንዲሆን በወር 530 ሺሕ ብር የሚከፈልበት ቤት ለመከራየት የተገባው ውል ተሰረዘ፡፡
ምንጮች እንደገለጹት፣ ፕሬዚዳንት ግርማ በቅርቡ ከቤተ መንግሥት ሲለቁ ከነቤተሰቦቻቸው እስከ ሕይወት ፍፃሜያቸው ይኖሩበታል ተብሎ የተመረጠውና በወር 530 ሺሕ ብር ለመክፈል ከቤቱ ባለቤት ጋር የተደረገው ስምምነት፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽሕፈት ቤት ቀርቦ ውል ታስሮበት ነበር፡፡ ሆኖም የኪራይ ስምምነቱ ውል ከተፈረመ ከሁለት ሳምንታት በኋላ የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት ውሉ እንዲቋረጥ መወሰኑን አስታውቋል፡፡ 
አዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ውስጥ የሚገኘውን ለፕሬዚዳንት ግርማ መኖሪያ የተመረጠውን ቤት ለመከራየት
ሙሉውን አንብብ-Read More

የኬኒያው አሳዛኙ እለልቂት

Geez Bet | Monday, September 23, 2013

የተመድ የናይሮቢዉን ጥቃት በጥብቅ አወገዘ

የተመድ የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት በኬንያ ናይሮቢ፤ ገበያ ማዕከል የተከሰተዉን ደም አፋሳሽ ጥቃት በጥብቅ አወገዘ። አሸባሪነት የዓለማቀፍን ሰላምና ጸጥታ የሚያደፈርስ ግዙፍ ጠንቅ ነዉ ሲል፤ በኒዮርክ የሚገኘዉ የተመድ ጽ/ቤት አስታዉቀዋል።
በናይሮቢ «ዌስት ጌት» በተባለ የገበያ ማዕከል በደረሰዉ አስከፊ ጥቃት እስካሁን 59 ሰዎች መገደላቸዉን እና ወደ 200 ሰዎች መቁሰላቸዉን የሀገሪቱ መንግስት አስታዉቋል።
ከሟቾቹ መካከል የዉጭ አገር ዜጎች ይገኙበታል። የኬንያ ፖሊስ እንዳስታወቀዉ ትናንት ቅዳሜ 18 ጨንበል ያጠለቁ ታጣቂዎች፤ ዊስት ጌት በተሰኘዉ፤ የገበያ ማዕከል ሰርጎ በመግባት የተኩስ ሩምታ ከፍተዋል። የእጅ ቦንብ አፈንድተዉ ከባድ ጥቃት አድርሰዋል። በመገበያያ ማዕከሉ አጋቾች ቦታውን በመቆጣጠር፤ ከፖሊስ ጋር ከበድ ያለ የመሳሪያ ልውወጥ ማድረጋቸውን እና ዛሬ
ሙሉውን አንብብ-Read More

አፍሪካና የማያባራው እልቂት

Geez Bet | Monday, September 23, 2013
የውጭ ሀገር ዜጎች ጥላቻ ዳግም በደቡብ አፍሪቃ መቀስቀሱ፣ በፍፁማዊ የዘውድ አገዛዝ በምትመራው አነስተኛዋ የአፍሪቃ ሀገር የምርጫ ሂደት፣ እንዲሁም ሶማሊያን የሚመለከት ጉባኤ በብራስልስ የተሰኙት ርዕሰ ጉዳዮች በትኩረት በአፍሪቃ ዝግጅታችን ከተካተቱት ጥንቅሮች ዋነኖቹ ናቸው።
ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ፖርት ኤሊዛቤዝ በተሰኘው አካባቢ የውጭ ሀገር ጥላቻ የተጠናወታቸው ግለሰቦች ሰሞኑን የሶማሊያውያን የሆኑ ንብረቶችን ሲመዘብሩ፣ ሲዘርፉ ብሎም እሳት ሲለቁባቸው ቆይተዋል። ከ1200 የሚበልጡ ሶማሊያውያንም ለህይወታቸው በመስጋት ቤት ንብረታቸውን ጣጥለው በሽሽት ላይ ይገኛሉ። አብዛኞቹም ታሪክ እራሱን እንዳይደግም አጥብቀው ሰግተዋል። የዛሬ አምስት ዓመታት ግድም
ሙሉውን አንብብ-Read More

Sep 18, 2013

መርዘኛ የጋዝ ጦር መሣሪያዎች

Geez Bet | Wednesday, September 18, 2013
ሰዎች ካለፈ እጅግ መጥፎ ድርጊት ፣ እስከምን ድረስ ትምህርት ይቀስማሉ? በተለያዩ ዘመናት ያጋጠሙ ሁኔታዎችን ፤ ጦርነቶችን ፤ ወረራዎችን ፤ ውዝግቦችን ስንመረምር ፣ ሰው፤ ጭካኔ የሚያሳይባቸው መሣሪያዎች በሥነ ቴክኑኒክ ተሻሽለው ተሠርተው ከመቅረባቸው 
በስተቀር፤ እርሱ ራሱ የባህርይ ለውጥ ያሳየበት ሁኔታ የለም። በቅዱሱ መጽሐፍ እንደተገለጠው ፤ ቃየል ብቸኛ ታናሽ ወንድሙን፤ አቤልን በድንጋይ ቀጥቅጦ ነው የገደለው። የዛሬው ዘመን ሰው «ወንድሙ» ን ፣ በአብራሪ- የለሽ አኤሮፕላን፣ ወይም በሚሳይል ወይም በመርዘኛ ጋዝ ማጥፋት ይችላል።
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኀን፤ ሰሞኑን በተደጋጋሚ ካነሱአቸው ጉዳዮች አንዱ በሶሪያ ፣ ረቡዕ ፤ ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ ም፤
ሙሉውን አንብብ-Read More

Sep 4, 2013

የሶሪያ ጦርነትና የኃያሉ ዓለም ዝግጅት

Geez Bet | Wednesday, September 04, 2013

ፕሬዝዳት ኦባማ የሚተማመኑበትን እቅዳቸዉ ለማስፈፀም-የሚተማመኑበትን ዘመናይ ጦር ከምርጥ መሳሪያዎቹ ጋር አዝምተዋል።የሶሪያ የቅርብ ወዳጆች ሩሲያ፥ ቻይና እና ኢራን የድብደባዉን ዕቅድና ዘመቻ አጥብቀዉ ይቃወማሉ።የሩሲያዉ ፕሬዝዳት ቭላድሚር ፑቲን ከዚሕም አልፈዉ አሜሪካና የተባባሪዎችዋን አቅድ አጣጥለዉ ነቅፈዉታል።
ሶሪያዎች ሠወስት ዓመት እንደለመዱት ይተለላለቃሉ።ለንደኖች፥ የደማስቆ መንግሥትን በኬሚካዊ ጦር መሳሪያ ሕዝብን በመጨረስ ወነጀሉ፥ ሶሪያን ለመብደብ ዛቱ፥ ፎከሩና በስተመጨረሻዉ ገሸሽ-ገለል አሉ።ፓሪሶች እንደ ለንደን፥ ዋሽግተኖች ዛቱ ፎከሩና የድብደባ-ነጋሪቱ ዋሽንግተን ላይ እስኪጎሰም አድፈጠዉ ቀሩ።ዋሽግተኖች እንደፎከሩ
ሙሉውን አንብብ-Read More