Time in Ethiopia:

Aug 19, 2013

በግብጽ አስከሬን፣ ቤቴክርስቲናያት እና መስጊድ በእሳት እየተቃጠሉ ነው!

Geez Bet | Monday, August 19, 2013
   
ግብፅ ጥይት፥ አረር፥ እየዘራች፥ አስከሬን-አጭዳ በእሳት ታጋያለች።ያቺ አስከሬን ለዝንታ-ዓለም የሚቀመጥባት ሐገር ዛሬ የሰዉ አካል ይተለተልባታል።ያቺ የጥንታዊ ሥልጣኔ ጎተራ፥ ያቺ የታሪካዊ የቅርስ ቋት፥ ያቺ ሥልታዊት ሐገር ታወረች? ወይስ አበደች? እዉሩ ወይም እብዱስ ማነዉ?
የግብፅ ጦር ዘመን ባፈራዉ ዘመናይ ጦር መሳሪያ መግደል፣ መደብደብ ማሰሩን፣ ሙስሊም ወንድማማቾች እምነት፣ቁጭት ና እልሕ በወለደዉ ፅናት መፋለሙን እንደቀጠሉ ነዉ።የዘመኑ ፈርዖኖች ፍሊሚያ የፈረዕኖቹን ዉልድ እየፈጀ፣ የፈርዖኖቹን ታሪካዊ፣ ሥልታዊት ሐገርን እያወደመ-ቁል ቁል ያንደረድራታል።የጥፋት ዉድመቱ ሒደት፣ ዉጤት መዘዝ አረብ አይሁድን፣ አፍሪቃ እስያን፣ ከሁሉም በላይ አዉሮጳ አሜሪካን እያሳሰበ ግን አቋማቸዉን እያዋዠቀ ነዉ።የግብፅ እልቂት-ዉድመት መነሻ የሁለቱ ፈርዖኖች ደምሳሳ ቅኝት ማጣቀሻ፣ የተቀረዉ ዓለም አቋም መድረሻችን ነዉ ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
ሙሉውን አንብብ-Read More

Aug 12, 2013

በአዲስ አበባ ግብረሰዶም በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ነው!

Geez Bet | Monday, August 12, 2013
 Addis Admass 
*ግብረሰዶማዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ “ሬንቦ” የተባለ ማህበር አቋቁመዋል
*በግብረሰዶማውያን ዙርያ የተካሄዱ ጥናቶች አዳዲስ መረጃዎችን ይፋ አድርገዋል
*ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የጥቃት ሰለባ ሆነዋል
*ኢትዮጵያውያን ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ ሲፈፅሙ የሚያሳዩ ፊልሞች ለገበያ ቀርበዋል
            ከወራት በፊት እዚህ አዲስ አበባ ከተማችን ውስጥ የተፈፀመ ታሪክ ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመው በአንድ ስመ-ጥር የወንዶች ልብስ መሸጫ ቡቲክ ውስጥ ነው፡፡ ወጣቱ በቡቲኩ ውስጥ ተቀጥሮ መስራት ከጀመረ ቆየት ብሏል፡፡ በአለባበሱ ሽቅርቅርና ዘመናዊ ነው፡፡ ወደ ቡቲኩ የሚመጡትን ደንበኞች በፈገግታና በትህትና እየተቀበለ ያስተናግዳል፡፡ ደንበኞች የፈለጉትን ልብስ አስወርደው ለመለካት ወደ መልበሻ ክፍል ሲገቡ በዓይኑ ይከተላቸዋል፡፡ በገቡበት የመልበሻ ክፍል መጋረጃ ላይ አይኖቹን
ተክሎ ለደቂቃዎች እንደሚቆይ የቡቲኩ ባለቤት ብዙ ጊዜ ታዝቦታል፡፡ ሆኖም ደንበኞቹ አዲሱን ልብስ ለብሰው ሲወጡ ለማየት ከመጓጓት የተነሳ እየመሰለው በዝምታ ያልፈዋል፡፡ “ለምን እንዲህ ታያለህ?” ብሎ ጠይቆት አያውቅም
ሙሉውን አንብብ-Read More

Aug 6, 2013

“ሹገር ማሚዎች” የከተማችንን ጎረምሶች እያጠመዱ ነው

Geez Bet | Tuesday, August 06, 2013
መታሰቢያ ካሣዬ 
 
የሴትየዋ የፊት ገፅታ የዕድሜያቸውን መግፋት ቢያጋልጥም በተለያዩ ሜካፖችና ቅባቶች እንዲሁም በዘመናዊ አለባበሣቸው ወጣት ለመምሰል ጥረዋል። እንዲህ ያሉ ወይዘሮዎች በአብዛኛው አንቱ መባልን አጥብቀው እንደሚጠሉ ያውቃል። ለዚህም ነው “አንቺ” እያለ ማናገር የጀመረው። አዲሷ የጂም ተማሪ፣ ወጣቱ ላይ ዓይናቸውን ጥለዋል፡፡ ዘንካታነቱና የስፖርተኛ ቁመናው ማርኳቸዋል፡፡
   የተስተካከለ ቁመናውና የስፖርተኛ አቋሙ የብዙ ሴቶችን ዓይን ይስባል፡፡ ጐተራ አካባቢ በሚገኝ አንድ ጂምናዚየም ውስጥ ተቀጥሮ ደንበኞቹን ስፖርት ያሰራል፡፡ በተግባቢነቱ፣ በተጨዋችነቱና በሰው አክባሪነቱ ሁሉም ይወዱታል፡፡ ከሥራው ቦታ ሳይርቅ ጎተራ ላንቻ አካባቢ ከግለሰብ በተከራየው አንድ ክፍል ቤት ውስጥ እየኖረ ሳለ ነው ህይወቱን የሚቀይር አንድ አጋጣሚ የተፈጠረው፡፡ ያቺን ዕለት አይረሳትም፡፡ ሴትየዋ ጠና ያሉ ናቸው - ከ50 ዓመት በላይ ይሆናቸዋል፡፡ የተደላደለ ኑሮ እንዳላቸው ሁለመናቸው ይናገራል፡፡ የጂም ደንበኛ ሆነው ሲመዘገቡ ምንም የተለየ ነገር ይፈጠራል ብሎ አላሰበም፡፡ እንደ ሁልጊዜው በፈገግታና በትህትና ተቀብሎ አስተናገዳቸው፡፡
የለበሰው ቲ-ሸርትና ቁምጣ በጡንቻዎቹ ተወጣጥሯል፡፡ አይናቸውን ከሱ ላይ መንቀል ተሣናቸው፡፡ በስፖርት ሰበብ መቀራረብና መነካካት መኖሩን ደግሞ ወደውታል፡፡ ከወገብሽ ጎንበስ እግርሽን ከፍ ክንድሽን ዘርጋ ከደረትሽ ገፋ እያለ ---የሚሰሩትን እንቅስቃሴ
ሙሉውን አንብብ-Read More