Time in Ethiopia:

Nov 30, 2013

ነገደ ኢትዮጵያ

Geez Bet | Saturday, November 30, 2013
ይህ ጽሑፍ መሪ ራስ አማን በላይ ‹የጥንቷ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ታሪክ› በሚል ርዕስ ከመጽሐፈ ሱባኤ ተረጎምኩት ብለው በ1985 ዓ.ም. ካሳተሙት መጽሐፍ ከምዕራፍ ሦስት በሙሉ የተወሰደ ነው፡፡ ጽሑፍ እሳቸው እንዳዘጋጁት ነው እንጂ የተጨመረበት ወይም ኤዲት የተደረገ ነገር የለውም፡፡ መጽሐፉ በያዛቸው መረጃዎችም ሆነ በምንጩ በተለምዶ ከሚታወቀው የታሪክ መጽሐፎች ይለያል፤ ስለ መጽሐፉ ይዘት፣ ምንጭና አስፈላጊነት ብዙ ማለት ቢቻልም፤ መጽሐፉ ብዙ ሰዎች በቀላሉ አግኝተውት ያላለነበቡት በመሆኑ አንዱን ምዕራፍ ብቻ እንደነበረ እንደማሳያ ማቅረብ የተሻለ መስሎ ታይቶኛል፡፡ ለማንኛውም ስለ መጽሐፉ ሁኔታ ለማወቅ በመግቢያውና በመጽሐፉ ጀርባ ከጻፉት ላይ ቀንጭቦ ማየት ጠቀሜታ ይኖረዋልና እነሆ!
(ከመግቢያው የተወሰደ)
‹‹ይሄን የጥንቷ የኢትዮጵያ ታሪክ ሱዳን አጥባራ በነበርኩበት ጊዜ የኢትዮጵያ ታሪክ ከመጽሐፈ ሲራክ እያነበብኩ ስለ ድንጋይ ጥበብና ስለሌላም ስከታተል እንደቆየሁ ጀቢል ኩራርና ጀቢል ኦባ ወደሚባለው ሃገር ሄጄ የጥንት ቤተክርስቲያን ፍርስራሽና የክርስቲያን መቃብር አገኘሁ፤ ከዚያም ጀበል ኦባ ለአንድ ሰባት ወር እንደተቀመጥኩ አንድ ሽማግሌ ሰው እንዲህ ካለ ዋሻ ውስጥ የክርስቲያኖች መጽሐፍ አለ ብለውኝ አብረን ሄድን፤ ብዙ በብራና የተጻፉና የተቀዳደዱ መጽሐፎች አገኘን፤ እንደገና ከሌላ ዋሻ ሄደን ስንቆፍር ብዙ ፅላቶችንና ቁርጥራጭ ካባዎችን፣ ቁመቱ ክንድ አንድ መቶ ስልሳ አራት ብራና የአክሱማይ ሲራክን መጽሐፍ፣ የሱባን ቋንቋና የሱባን ታሪክ የያዘ መጽሐፈ ሱባኤ፣ እንደዚሁም በጣም የረዳኝ ሁለት መቶ ብራና አራት መቶ ገጽ ያለው የኢትዮጵያ ነገሥታት ታሪክ ዘግዱር ዘእንዳ ቤት በተፈለፈለ የድንጋይ ጉድጓድ ከተልባና ከአመድ ጋር ተቀብሮ ተገኘ፡፡
መጽሐፈ ሱባኤ ከአዳም እስከ ቀዳማዊ ምኒልክ መፀሐፈ አክማይ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 29, 2013

አና ጐሜዝ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ገንቢና ግልጽ ውይይቶችን አደረግኩ አሉ

Geez Bet | Friday, November 29, 2013
ከዘጠኝ ዓመት በፊት በተካሄደው የግንቦት 1997ቱ ምርጫ የአውሮፓ ኅብረትን በመወከል የምርጫ ታዛቢ የነበሩት ፖርቱጋላዊቷ አና ጐሜዝ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር መነጋገራቸውን ገለጹ፡፡
ዛሬ በሚጠናቀቀው የአፍሪካ፣ የካሪቢያን፣ የፓስፊክና የአውሮፓ ኅብረት የጋራ የፓርላማ 26ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ለመካፈል አዲስ አበባ የመጡት አና ጐሜዝ፣ በአዲስ አበባ በነበራቸው ቆይታ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ገንቢና ግልጽ ውይይቶችን ማድረጋቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የጋራ ስብሰባው ላይ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ የመጡት የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ አባልና በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ከፍተኛ ትችት በመሰንዘር የሚታወቁት አና ጐሜዝ፣ ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ምንም ዓይነት የቪዛ ችግር እንዳልገጠማቸው ገልጸው ይህም አዲስ ዓይነት የፖለቲካ አተያይ እየተፈጠረ መሆኑን ያሳያል ብለዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

የሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና የሙሌት ፖሊሲው

Geez Bet | Friday, November 29, 2013
ጥንታዊ ስልጣኔን ለታሪክ ትተን ከድህነት ወለል በታች ከሚፈረጁት የዓለማችን ኣገራት ተርታ ተሰልፋ የምትገኘው ኢትዮጵያ ግን ደግሞ ይህ ነው የማይባል የተፈጥሮ ሀብትም እንዳላት ይታወቃል። 
  ከተፈጥሮ ሀብቷ መካከልም ኣንደኛው የውኃ ኃብቷ ሲሆን ወንዞቿ ደግሞ ድንበር ዘለልም ጭምር ናቸው። ከዚሁ የተነሳ የምስራቅ ኣፍሪካ የውኃ ምንጭ በመባልም ትታወቃለች። ኣንዱና ዋናው ደግሞ ጥቁር ዓባይ ወይንም በውጪው ኣጠራር ብሉ ናይል ነው። 75 በመቶ የሚሆነው የናይል ውኃም የሚመጣው
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 26, 2013

የኢራን ሥምምነትና ዉዝግብ

Geez Bet | Tuesday, November 26, 2013
ኢራን ድብቅ የኑክሌር ተቋም እንዳለት ከታወቀበት ከሁለት ሺሕ ሁለት ጀምሮ በቴሕራንና በምዕራባዉያን ሐገራት ፖለቲከኞችን መካከል የደራዉ ዉዝግብ ለመጀመሪያ ጊዜ-አንድ እልባት አግኝቷል። የእስራኤል-ምዕራባዉያን ልዩነት፥ የኢራን-እስራኤል ዉዝግብስ ነዉ?-የዛሬዉ ጥያቄ 
የአያቶላሕ ሩሑላሕ ሆሚኒዋ «ታላቅ ሠይጣን» የድብቅ ዲፕሎማቶች፥ ከጆርጅ ዳብሊዉ ቡሿ «የሰይጣን ዛቢያ» ስዉር መልዕክተኞች ጋር በዓለም የፖለቲካ መድረክ ብዙም በማትታወቀዉ ሐገር፥ በድብቅ ሆቴል፥ በዘወርዋራ አሳንስር ወይም ሊፍት ዉስጥ የጀመሩት ድርድር ቅዳሜ-ለዕሁድ አጥቢያ በይፋ ዉል ተቋጠረ።ዤኔቭ።
«ከከባድ ድርድር በሕዋላ ለረጅም ጊዜ፥ አጠቃላይ መፍትሔ በሚያደርሰን የጋራ የድርጊት መረሐ-ግብር ላይ ዛሬ ተስማምተናል።»
የአዉሮጳ ሕብረት የዉጪ ግንኙነት ሐላፊ ወይዘሮ ካትሪን አሽተን።የድብቅ፥ ይፋዉ ድርድር ሒደት፥ የስምምነቱ ይዘት፥ የተቃዉሞዉ እንዴትነት ያፍታ ዝግጅታችን ትኩረት ነዉ።አብራችሁኝ ቆዩ።
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 25, 2013

የሳኡዲ ተመላሾች የስደት መከራቸውን በምሬት ይተርካሉ

Geez Bet | Monday, November 25, 2013
እኛ ተርፈናል፤ እዛ ላሉት ድረሱላቸው
ኢትዮጵያውያን ሴቶች ተገደው እየተደፈሩ ነው !
እስር ቤት አንዲት ነፍሰ ጡር ሞታብናለች
- የስደት ተመላሾች 
ሳኡዲ አረቢያ በህገወጥ መንገድ ወደ አገሯ የገቡ ስደተኞችን በሃይል ማስወጣት
ከጀመረች ሁለተኛ ሳምንቷን ያስቆጠረች ሲሆን ህገወጥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደአገራቸው የመመለስ ዘመቻው አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ ዜጐችን ከሳኡዲ ለማምጣት ባለፈው ሳምንት በቀን ሰባት በረራዎች ይደረጉ እንደነበር ያስታወሱት የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤ በዚህኛው ሳምንት በቀን 12 በረራዎች እየተደረጉ ዜጐችን ማምጣቱ እንደቀጠለና እስከትላንት ድረስ ከ19ሺ በላይ ዜጐች መመለሳቸውን ገልፀዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ኢትዮጵያዊ ዋጋው ስንት ነው?

Geez Bet | Monday, November 25, 2013
(ተመስገን ደሳለኝ)
የዚህ ፅሁፍ ማጠንጠኛ የፖለቲካ አመለካከትን መተቸት አይደለም፤ ከዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ወረድ ያሉ የጉልበታሙን ስርዓት የሥራ አፈፃፀሞችን ማብጠልጠልም አይደለም፤ የተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ስንክሳር መንቀስም… አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ (አል-ሀበሽ) መሆን ለፈተና፣ ለመከራ፣ ለሰቆቃ… መዳረጉ የወለደው ብሶት እንጂ፤ መመረር-ማምረር ነው፡፡ …ይህ የእኛ ዕጣ ፈንታ የሆነበትን ምስጢር መመርመር ነው፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
ሰሞኑን የሳውዲ አረቢያ መንግስት ታጣቂዎች እና በድጎማ የሚያድሩ የሀገሬው ተወላጆች በመሰረቱት የጥፋት ግንባር ጉልበታቸውን ገብረው፣ በላብ በወዛቸው በሚያድሩ ስደተኛ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመው አረመኔያዊ ወንጀል፣ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ልብ በከባድ ሀዘን የሰበረ፣ በቁጭት ያንገበገበ አሳዛኝ ፍፃሜ ሆኗል፡፡ ጭፍጨፋው ሃይማኖታዊው

ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 24, 2013

አቶ ያረጋል አይሸሹም ከ5 የሙስና ክሶች በ4ቱ ነፃ ሆኑ

Geez Bet | Sunday, November 24, 2013
በተለያዩ ከተሞች በራሳቸው፣ በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ስም 17 ቦታዎችንና ቤቶችን ይዘዋል ከሚለው ክስ ነፃ ሆነዋል፡፡
ከባለቤታቸው ጋር ምንጩ ያልታወቀ 490ሺ ብር በባንክ አንቀሳቅሰዋል ከሚለው ክስ ነፃ ናቸው ተብሏል:: የቀድሞው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ያረጋል አይሸሹም፤ በፀረ ሙስና ኮሚሽን ከቀረቡባቸው አምስት ክሶች መካከል በአንዱ ብቻ “ጥፋተኛ ናቸው” የተባሉ ሲሆን፣ ምንጩ ያልታወቀ ሃብት አካብተዋል በሚል ከቀረበባቸው ክሶች ነፃ ሆኑ፡፡
አቶ ያረጋል አይሸሹም እና የትምህርት ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ ሃብታሙ ሂካ፣ ከሁለት የግል ድርጅት ሃላፊዎች ከአቶ ጌዲዮን ደመቀና ከቶ አሰፋ ገበየ ጋር “ጥፋተኛ ናቸው” የሚል ውሳኔ የተላለፈባቸው፤ ለሦስት የትምህርት ተቋማት ግንባታ ከወጣው ጨረታ ጋር በተያያዘ ክስ ነው፡፡ ህገወጥ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር  ለመምህራን ኮሌጅ፣ ለአዳሪ ት/ቤት እና ለቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የግንባታ ጨረታ ከመንግስት መመሪያ ውጪ እንዲከናወን አድርገዋል በሚለው ክስ 4ቱ ተከሳሾች ጥፋተኛ ሆነው እንደተገኙ የከፍተኛው ፍ/ቤት ችሎት ሐሙስ እለት ገልጿል፡፡ 
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 23, 2013

ኢህአዴግ ስለምን ይጮኻል?

Geez Bet | Saturday, November 23, 2013
(ተመስገን ደሳለኝ)
በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም በተፈጥሮ ሞት ነውና፡፡ በ1983 ዓ.ም ወርሃ ግንቦት በጠብ-መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ-መራሹ መንግስትም ቢሆን፣ በቀድሞዎቹ ገዥዎች ‹የብረት ጫማ› ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ-ስንብቱን በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል፡፡ ዕ
ለተ-ስንብቱ መቃረቡን የሚጠቁመው ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልክ እንደ ደርግ የመጨረሻዎቹ ወራት ሁሉ፣ ግንባሩና አጋር ፓርቲዎቹ ለየት ባለ መልኩ በራሳቸውና በሹማምንቶቻቸው ላይ በአደባባይ የተቃውሞ ድምፅ ማሰማት መጀመራቸው ነው፡፡ የዚህ ፅሁፍ ተጠየቅም ይህ ነውና ተጨባጭ እውነታውን ለማብራራት በቂ የሆኑ አስረጂዎችን በአዲስ መስመር በዝርዝር ለመመልከት እሞክራለሁ፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

የዓርብ ግዞተኞች

Geez Bet | Saturday, November 23, 2013
አስራት አብርሃም
የሳውዲ መንግስት በወገኖቻችን ላይ እየፈፀመ ባለው ግድያ እና ግፍ ምክንያት በሰማያዊ ፓርቲ የተጠራው ሰልፍ በመንግስት በእኩል ይሁንታ እንዳላገኘ ብንሰማም የሆነው ይሁን እነርሱ በሰው ሀገር መከራና ስቃይ እየተቀበሉ አይደለ በሚል ነው ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ወደ ሰልፉ ለመሄድ የቆረጥነው። ችግር ሊኖር እንደሚችል ገምተናል።
ከሰማያዊ ፓርቲ ብርሀኑ ተክለያሬድ ጋር የት ደረሳችሁ እየተባባልን እየተደዋወልን ነበርና በመሀሉ ስልኩ ጠፋኝ። መጨረሻው ግን አራት ኪሎ እንደታገቱ ሰማንና እኔና ሌሎች ሶስት ጓደኞቼ ሆነን ወደ ሰልፉ ቦታ መሄድ ጀመርን። ከኋላችን ብዙ ሰው ቀስ እያለ እየመጣ ነበር። ወደ ሰልፉ እየተጠጋን ስንመጣ ብዙ ሰው ወደእኛ አከባቢ እየሸሸ ሲመጣ ተመለከትን። የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ወጣት ሴት ልጆች እያለቀሱ ወደ እኛ እየመጡ ነው። በዚህ ጊዜ እነ ዳዊት ከበደ፣ ኤልያሰ ገብሩ እና እስክንድር ፍሬው አግኝተናቸው ስለሁኔታው
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 22, 2013

የአፍሪቃና የአውሮፓ የሰብዓዊ መብቶች ውይይት

Geez Bet | Friday, November 22, 2013
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች በአንዳንድ የአፍሪቃ ሃገራት በመገናኛ ብዙሃንና በሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ላይ ተጠናክሮ የቀጠለው ጥቃት እንዲቆም እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ብራሰል ቤልጂግ ውስጥ ለተካሄደው የአፍሪቃና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽኖች የሰብዓዊ መብቶች የጋራ መድረክ አሳስቧል ። 

የአፍሪቃ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት በአፍሪቃ ለሰብዓዊ መብት መከበር ለሚታገሉና አውሮፓ ውስጥ ለሚገኙ የውጭ ዜጎች የተጠናከረ ጥበቃ ለማድረግ በጋራ እንዲሰሩ ተጠየቁ ። የአውሮፓ ህብረትም ለውጭ ዜጎችና ለተገን ጠያቂዎች የተሻለ ጥበቃ እንዲያደርግ ጥሬ ቀርቦለታል ። ሂሩት መለሰየአፍሪቃ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት ኮሚስዮኖች ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ ካካሄዱት ዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶች ውይይት ዋነኛ ትኩረቶች አንዱ አፍሪቃ ውስጥ በሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች በጋዜጠኖችና በሲቪል ማህበራት ላይ የሚፈፀመው ጥቃት
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 21, 2013

የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጤንነት እያነጋገረ ነው

Geez Bet | Thursday, November 21, 2013
- «ፕሬዚዳንቱ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ» አቶ የማነ ገብረመስቀል
- አሜሪካ ዜጎችዋ ወደ ኤርትራ እንዳይጓዙ አስጠነቀቀች
ከመገናኛ ብዙኃንና ከሕዝብ እይታ ከራቁ ከአንድ ወር በላይ የሆናቸው  የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጤንነት ጉዳይ እያነጋገረ ነው፡፡

አስማሪኖ የተባለውና መቀመጫውን በካሊፎርኒያ አሜሪካ ያደረገው የኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚ ድረ ገጽ እንደጻፈው፣ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ከወትሮው በተለየ ከመገናኛ ብዙኃን ርቀዋል፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ለመጨረሻ ጊዜ በሚዲያ የታዩት ጥቅምት 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በተካሄደው የምሥራቅ አፍሪካ የአንበጣ መቆጣጠሪያ ድርጅት የሚኒስትሮች ምክር ቤት 58ኛ ጉባዔ ላይ መሆኑን ድረ ገጹ ጽፏል፡፡
ከዚያም በጥቅምት 20 ቀን 2006 ዓ.ም. በጉበት ሕመም ምክንያት አስመራ በሚገኘው የአየር ኃይል ሐኪም ቤት ለስድስት ሰዓታት ያህል ሕክምና ተደርጐላቸው  ወደ ቤተ መንግሥት መመለሳቸውን ጽፏል፡፡ በመቀጠልም ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ወይም ኳታር ለተጨማሪ ሕክምና መሄዳቸው እንዳልቀረ አትቷል፡፡
ስለ ጉዳዩ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ የማነ ገብረመስቀልን በትዊተር ገጻቸው ለሪፖርተር ማብራሪያ እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ «አስቂኝ ቅዠት ነው» የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
«ፕሬዚዳንቱ በመልካም ጤንነት ላይ ናቸው፤» በማለት መሠረተ ቢስ የሆነ ወሬ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ «ምንም አዲስ ነገር የለም፡፡ አስማሪኖ ውሸት ማውራት ስለፈለገ ነው፡፡ ማንኛውንም የአስመራ ነዋሪ መጠየቅ ይቻላል፤ ምክንያቱም ፕሬዚዳንቱ ወደ ቢሮአቸው ሲገቡ ያዩአቸዋል፤» ብለዋል፡፡
 ከዚህ ቀደም ከሚያዝያ 4 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ከአንድ ወር በላይ ከመገናኛ ብዙኃን መጥፋታቸው መነጋገሪያ እንደነበር ይታወቃል፡፡ 
በተያያዘ ዜናም የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የቆንስላ ጉዳዮች ቢሮ ከትላንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ፣ የአሜሪካ ዜጎች ወደ ኤርትራ ምንም ዓይነት ጉዞ እንዳያደርጉ ጠንከር ያለ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ በአገሪቷ ላይ የሚታየውን የፀጥታ ችግር እንደ ምክንያት በመግለጽ ከአሁን በፊት በግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም. ያወጣውን የጉዞ ማዕቀብ ማስጠንቀቂያ አጠናክሯል፡፡
ስቴት ዲፓርትመንት በመግለጫው እንዳስታወቀው፣ የአሜሪካና የኤርትራ ድርብ ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች ያለምንም ምክንያት እየታሠሩ ነው፡፡ በተጨማሪም በመርከብ የሚጓዙ የአሜሪካ ዜጎች በኤርትራ የባህር ዳርቻ እንዳይጓዙና መልህቆቻቸውን እንዳይጥሉ ጠንከር ያለ ማሳሰቢያ አስተላልፏል፡፡ 
የኤርትራ መንግሥት መቀመጫው ሶማሊያ ለሆነው የአልሸባብ አክራሪ ቡድን ድጋፍ ያደርጋል በማለት የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በታኅሳስ 14 ቀን 2002 ዓ.ም. የመሣሪያ ማዕቀብ መጣሉ ይታወቃል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት የሶማሊያና የኤርትራ አጣሪ ኮሚቴ ግን የኤርትራ መንግሥት ለአልሸባብ «ቀጥታ» ዕርዳታ እንደማያደርግ ሐምሌ 9 ቀን 2004 ዓ.ም. አስታውቋል፡፡
Source: http://www.ethiopianreporter.com
 
ሙሉውን አንብብ-Read More

የኢትዮጵያውያን ከሳ/አረቢያ መውጣት ያስከተለው ችግር

Geez Bet | Thursday, November 21, 2013
እአአ ከ 610 ዓ ም ጀምሮ የእስልምና ኃይማኖት መገኛ እና ማስፋፊያ ማዕከል በመሆን ትታወቃለች። በማዕከላዊው ምስራቅ በፋርስ ባህረ ሰላጤ እና በቀይ ባህር መካከል በተንጣለለው የዓረቢያ በረሃ ላይ ጆርዳን ኢራቅ ኩዌት የመን ኦማን ቀጠር እና የተባበሩት ኣረብ ኢማራት በምድር ያዋስኗታል። 
ቀድሞ ኢትዮጵያ ኣሁን ግን ከኤርትራም ጋር የባህር ማዶ ጎረቤት ናቸው። ኣሁን ያለውን ኣገራዊ ቅርጽ ይዛ በኣዲስ መልክ እንደ መንግስት የቆመችው ከ 1818 ዓ ም ጀምሮ ሲሆን ስያሜዋንም ያገኘችው እ ኣ ዘ ኣ በ 1932 ዓ ም በንጉስ አብዱልአዚዝ አል ሳዑዲ ኣማካኝነት በንጉሱ የቤተሰብ ስም ተሰይማ መሆኑ ይተረክላታል። ሳዑዲ ዓረቢያ።
በነዳጅ ዘይት ምርቷ በዓለም ቀዳሚነቱን ይዛ የምትገኘው ሳውዲ ኣረቢያ የቆዳ ስፋቷ 2 ሚሊየን ስ ኪ ሜ ገደማ ሲጠጋ በ2010 በተካሄደ ቆጠራ መሰረት 27,5 ሚሊየን ያህል ህዝብም ኣላት። ከእነዚህ መካከል 19 ሚሊየኑ ብቻ የሳውዲ ዜጎች ሲሆኑ ቀሪው ስምንት ሚሊየን ደግሞ በተለያዩ ጊዜና ሁኔታዎች ወደ ኣገሪቱ የገቡ የውጪ ዜጎች መሆናቸው ነው። ከእነዚህም መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ህጋዊ የኣገር መኖሪያ እንደሌላቸው ሲገመት ለሰሞኑ ኣስደንጋጭ ክስተትም ምክኒያት የሆነው ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት እነዚህኑ ስደተኞች የማስወጣቱ ዘመቻ ነው።
ጤና ይስጥልኝ የተወደዳችሁ የዶቸቬሌ ታዳሚዎች በዕለቱ የማህደረ ዜና ዝግጅታችንም ይህንኑ ዘመቻ ከኢትዮጵያ ኣንጻር ለመዳሰስ እንሞክራለን።
ዘውዳዊው የሳውዲ አረቢያ መንግስት በዚህ ጊዜ የዚህ ዓይነት ግራ የተጋባ ጭፍን እርምጃ ለመውሰድ የተገደደው ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደሚጠቁሙት ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በዓረቡ ዓለም የተቀጣጠለውን እና ከቱዚያ ጀምሮ ሊቢያን እና ግብጽን ያናወጠውን እንዲሁም በጎረቤት የመን ኣድርጎ እስከ ኣሁንም ሶርያን በማተራመስ ላይ ያለውን ብሶት ወለድ የዓረብ ኣብዮት ተከትሎ ከወዲሁ ለዜጎቿ የስራ ዕድል ለመክፈት ታስቦ ነው ተብሏል።
በዚሁ መሰረት የሪያድ ኣገዛዝ ህጋዊ የመኖሪያ እና የስራ ፈቃድ የሌላቸው የውጪ ዜጎች ኣንድም ሰነዶቻቸውን እንዲያስተካክሉ ኣልያም ኣገሪቱን ለቀው እንዲወጡ የ ሰባት ወር የእፎይታ ጊዜ መስጠቱ ይታወሳል። በዚህ ጊዜ ውስጥም በሳውዲ ምንጮች መረጃ መሰረት 4 ሚሊየን ያህል የውጪ ዜጎች ሰነዶቻቸውን ኣስተካክሏል። 1 ሚሊየን ገገማ ደግሞ ኣገሪቱን ለቀው መውጣታቸው ታውቐል።
የተጠቀሰው የምህረት ጊዜ ያበቃው እ ኣ ዘ ኣ ባለፈው ህዳር 3 ቀን ሲሆን ወዲያውኑ በሺዎች የሚቆጠሩ የሳውዲ ፖሊሶች በእነሱ ኣጠራር ሹርጣዎች በየአካባቢው ተሰማርተው የውጪ ዜጎችን ማሳደድ ጀመሩ። ምንም እንኩዋን እንደ ወትሮው ወደ ጎዳና የወጣ ስደተኛ ባይኖርም በስራ ቦታው እና ከየመኖሪያ ቤቱም እየገቡ ስደተኞችን ማደኑ ቀጠለ። ኣያያዙም ኃይል የተቀላቀለበት እና ስደተኞቹ እንደሚሉት ፍጹም ጭካኔ የተሞላበት ነው የነበረው።
ከፖሊስ ኃይሉ በተጨማሪ ግርግር ለሌባ ያመቻል እንዲሉ ጋጠ ወጥ የሳውዲ ወጣቶች የፖሊሶቹን ዱካ እየተከተሉ እና ቤት ሰብረው እየገቡ ገንዘብ እና ንብረት መዝረፍ ወንዶችን መደብደብ እና ሴቶችን መድፈሩን ተያያዙት። ምንም እንኩዋን ከየአቅጣጫው የሚወጡት ዘገባዎች እርስ በርሳቸው የሚጣለዙ ቢሆኑም እስከኣሁን በመቶዎች የሚቆጠሩ የአካል ጉዳት ደርሶባቿል። ጥቂት የማይባሉ ደግሞ ህይወታቸውን ኣቷል።
ይህ ሁሉ ሲሆን ግን ከስደተኞቹ አንደበት መረዳት እንደተቻለው ማሳደዱም ሆነ ጭካኔው የበረታው በተለይ በኢትዮጵያውያኑ ላይ ነው ተብሏል።
የሴቶቹ እሮሮ ደግሞ በእርግጥም ለየት ያለ እና ዘግናኝም ነው።
የሴት ኢትዮጵያውያን መደፈር በአሰሳው ወቅት በሚደርስባቸው ብቻም ኣልተወሰነም። ተይዘው ወደ ማጎሪያ ካምፕ ከተወሰዱ በኃላም ከካምፑ ተሰርቀው ይወሰዳሉ ተብሏል።
በዚያ ላይ የማጎሪያ ካምፑ እስረኞችም ቢሆኑ ለበረኃ ግመሎች ካልሆነ በስተቀር የሰው ልጅ ማቆያ ኣይመስልም የሚሉት የሪያድ እስረኞች ከዚሁ የተነሳ በርካታ ህጻናት እና እናቶች መታመማቸውንም ይናገራሉ።
በዚህ ጭፍን ዘመቻ ወቅት እጅግ ኣነጋጋሪ ከሆኑት ነገሮች መካከል የሳውዲ ወጣቶች በነቂስ ወተው ፖሊሶችን መከተል እና ስደተኞችን መዝረፍ መደብደብ እና በተለይ ሴቶችን የመድፈሩ ጉዳይ ነው።
የተገደሉትን ስደተኞች ቁጥር ኣስመልክቶም ከኢትዮጵያ እና ሳውዲ መንግስታት የወጡ ዓኃዞች ከሞላ ጎደል ተቀራራቢ ቢሆኑም ዘገባዎች ግን ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችል ይጠቁማሉ።
«ነሲም በተባለች ከዚህ ከሪድ ኣንድ 30 እና 50 ኪ ሜ ርቃ በምት ገኘው ከተማ ባለፈው ሐሙስ ምሽት የሳውዲ ፖሊሶች ግርግር ፈጥረው 3 ሰዎችን ገግሏል። ሶስቱም ኢትዮጵያውያን ናቸው። ብዙ ሰው እኮ ነው የተገደለብን። ሰው ሲገደል ወዲያውኑ ኣንስተው ወደማይታወቅበት ቦታ ስለሚወስዱት ለጊዝው ኣይታወቅም እንጂ በጣም ብዙ ሰው ነው የተገደለው። እኔ እራሴ የማውቃቸው ከአስር ሰው በላይ እገሌ እገሊት ብዬ ልቆጥርልህ እችላለሁ።»
እስከ ኣሁን ከ 3000 በላይ ስደተኞች ኣገር ቤት ደርሷል እየተባለ ባለበት በኣሁኑ ወቅትም ከተደበቁበት ገና ያልወጡ እና ባሉበትም በረኃብ እየተቸገሩ ያሉም እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል።
ለዚህ ጭፍን እርምጃ የሳውዲ አረቢያን መንግስት መኮነናቸው ባይቀርም ስደተኞቹም ሆኑ በርካታ ኢትዮጵያውናን ይበልጥ የሚያማርሩት ግን ሪያድ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኢምባሲን እና የኢትዮጵያን መንድስትም ጭምር ነው ነው።
የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን ጉዳይ ከልብ እያየው ኣይመስለንም። እንዲያውም ውስጥ ውስጡን ከሳውዲዎች ጋር እየሰራ ያለ ነው የሚመስለው የኢትዮጵያ መንግስት። ኢምባሲው በተለይ ልክ የዚህ ኣገር ፖሊሶች ገድለው ኣስክሬን እንደሚደብቁት እሱም አብሮ እየደበቀ ነው እንጂ ይህንን ጉዳይ ፈጽሞ በትኩረት እያየው ኣይደለም።
የሳውዲዎች ዘመቻ በተለይ በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ ማተኮሩን ኣስመልክቶ የኢትዮጵያው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እርምጃውን ማውገዙ የሚታወስ ሲሆን ቃል ኣቀባዩ ኣምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለዶጨቤሌ እንደገለጹት ስደተኞቹን ወደ ኣገራቸው የመመለሱ ሂደት በተቻለፍጥነት እየሄደ ነው።
የሆነ ሆኖ በሪያድ የኢትዮጵያ ኢምባሲም ሆነ ከአዲስ ኣበባም የኃይለማሪያም ደሳለኝ ኣስተዳደር በኣጠቃላይ ከዘመቻው በፊትም ሆነ ከዚያ ወዲህ ዜጎቹን ለመታደግ የወሰዷቸው እርምጃዎች በቂ ኣይደሉም ሲሉ ብዙዎች ይከሳሉ። በዚሁ ምክኒያት ጭምር ይመስላል በዓለም ዙሪያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ከዚያ ወዲህ በቁጣ ገንፍለው ዋሽንግተን ዲ ሲ ን ጨምሮ በተለያዩ የአሜሪካ እና የኣውሮፓ ከተሞች አደባባይ ወቷል። ወደ ሳውዲ ኢምባሲ እየሄዱም ተቃውሞኣቸውን ኣሰምቷል።
በኣገር ቤት የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ኣድራጎቱን በመኮነን መግለጫ ኣውጥቷል። ባለፈው ዓርብ ስማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰልፍ ግን አዲስ ኣብባ ላይ ልክ እንደ ሪያድ በሳውዲ ፖሊስ ሳይሆን ግን በኢትዮጲያ ፖሊሶች እርህራሄ በሌለው ድብደባ መበተኑ በኣሳኝነቱ ተዘግቧል።
በተያያዘ ዜና የሰሞኑ የሳውዲ አረቢያ እርምጃ ታሪካዊ ስህተት ነው የሚሉ ወገኖችም ኣሉ። ኣንዱም ሼክ ነጂብ መሐመድ ሲሆኑ በዋሽንግተን ዲ ሲ የሚኖሩት ሼክ ነጂብ በኣሁኑ ጊዜ « ዘ ፈርስት ሂጂራ» የተባለው ዓለም ዓቀፍ መንግስታዊ ያልሆነ የኢትኆጵያውያን እስላማዊ ተቐም መሪ ናቸው።
በእስልምና ኃይማኖት እንግዳ ይከበራል እንጂ ኣይነካም የሚሉት ሼክ ነጂብ በእስላማዊው የሸሪኣ ህግ እመራለሁ የሚለው የሳውዲ ኣገዛዝ ይህንን በማድረጉ ተጠያቂ ከመሆን ኣያመልጥም ይላሉ።
ጃፈር አሊ
አርያም ተክሌ
Source: www.dw.de

ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 17, 2013

ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በፀጥታ ሀይሎች ከሸፈ

Geez Bet | Sunday, November 17, 2013
በርካታ ሰዎች ተደብድበዋል በላንቻ ፖሊስ ጣቢያ ከ70 በላይ ሰዎች ታስረዋል
በሳኡዲ አረቢያ በኢትዮጵያዊያን ላይ እየደረሰ ያለውን ግድያና እንግልት ለመቃወም በትላንትናው እለት ሰማያዊ ፓርቲ ጠርቶት የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በፀጥታ ሀይሎች የከሸፈ ሲሆን፤ ለሰልፉ የወጡት ሰዎች፣ መንገደኞች፣ በተለያየ ምክንያት ጥቁር የለበሱና ሌሎችም ድብደባ ደርሶባቸዋል፡፡ ጋዜጠኞችን ጨምሮ ከሰባ በላይ ሰዎች በላንቻ ፖሊስ ጣቢያ ታስረዋል፡፡
በድብደባው ሲቪል የለበሱ የፀጥታ ሃይሎችም እንደተጐዱ የላንቻ ፖሊስ ጣቢያ ሀላፊ ገልፀዋል፡፡ ሰልፉን የጠራው ፓርቲ አመራሮች ከፅፈት ቤታቸው ሳይወጡ መታሰራቸው የተሰማ ሲሆን የሳኡዲ አረቢያ ኤምባሲ አካባቢ በፌደራል እና በአዲስ አበባ ፖሊስ ተከቦ ውሏል፡፡ ወደ ኤምባሲው የሚጠጋ፣ ሰብሰብ ብሎ የቆመ፣ ፎቶ ሲያነሳ የተገኘና ሌሎችም በፖሊስ ነጭ ፒክ አፕ መኪና እየተጫኑ ላንቻ አካባቢ በሚገኘው የወረዳ 18 ፖሊስ የተወሰዱ ሲሆን፤ ፖሊስ ጣቢያ ከገቡት ውስጥ የ70 አመት አሮጊት እና የ62 አመት አዛውንት ይገኙበታል፡፡
“ምንም የማውቀው ነገር የለም፤ ከልጄ ጋር መንገድ እየሄድኩ ነው የተያዝኩት” ብለዋል፤ የ70 ዓመቷ አሮጊት፡፡ ከታሰሩት መካከል በድብደባ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ኢዮብ አርጋው የተባለ ወጣት፤ አብረውት በታሰሩት ሰዎች ጉትጐታና ለቅሶ ፖሊስ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ወስዶታል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ረቡዕ ማታ በሰጠው መግለጫ፤ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ አራት ዋና ዋና ነገሮች እንደሚከናወኑ ገልፆ ነበር፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ የሚወጡ ሁሉ በሳኡዲ የሞቱትን፣ የታሰሩትን እና የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሰብና ሀዘናቸውን ለመግለጽ ጥቁር እንዲለብሱና ጥቁር ሪቫን ክንዳቸው ላይ እንዲያስሩ፣ ሙስሊሙ በዕለቱ በጁምአ ሶላት እንዲፀልይ እንዲሁም፣ በሳኡዲ ኤምባሲ በር ላይ ተቃውሞ ከመሰማቱ በፊት ለሞቱት የህሊና ፀሎት ለማድረግና በሳኡዲ አረቢያ እየደረሰ ስላለው አጠቃላይ ጉዳት የሚያትት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ጽሑፍ ቀርቦ ሰልፉ እንደሚበተን ገልፆ ነበር።
ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ ፓርቲው ለከተማው መስተዳድር በደብዳቤ ማሳወቁን እና መስተዳድሩ ምላሽ አለመስጠቱን፤ ይህ ደግሞ ሰልፉ መፈቀዱን የሚያሳይ እንደሆነ ኢ/ር ይልቃል ቀደም ብለው ገልፀው ነበር፡፡ የፓርቲው አባላት እንደገለፁት፤ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃልን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ለሰልፉ ከፓርቲው ጽ/ቤት ሳይወጡ ነው በፖሊስ የተወሰዱት፡፡ በስፍራው ተገኝተን እንደታዘብነው “ልጆቻችን ታረዱ ተገደሉ” እያሉ የሚያለቅሱ እናቶች የነበሩ ሲሆን “ፖሊስ በህዝቡ ላይ ድብደባና እንግልት ማድረሱ አግባብ አይደለም፤ ይህ ኢትዮጵያ ሳይሆን ሳኡዲ ማለት ነው” ሲሉም ተደምጠዋል፡፡ “ፎቶ አንስታችኋል” በሚል ከሌሎች ሰዎች ጋር በፖሊስ ተይዘው ወረዳ 18 ላንቻ ፖሊስ ጣቢያ ከስድስት ሰዓት እስከ ስምንት ተኩል ቆይተዋል፡፡
በፖሊስ ጣቢያው ውስጥ ከነበሩት መካከል አብዛኞቹ መንገደኞችና ስለጉዳዩ ምንም እንደማያውቁ ተናግረዋል፡፡ ከቀኑ ስምንት ሰዓት አካባቢ ጋዜጠኞች ብቻ ተጠርተን የጣቢያው ሃላፊ ያነጋገሩን ሲሆን፤ “ሰልፉ አልተፈቀደም፣ ህገወጥ ነው፤ ህዝቡ ኤምባሲውን ሰብሮ ሊገባ ሲል ዝም ብሎ ማየት አይቻልም፣ ነገሩን በክፉ አትዩት ጉዳዩን የኢትዮጵየ መንግስትና የአለም መንግስታት እየተከታተሉት ነው” በማለት ካሜራችንን እና መታወቂያችንን የመለሱልን ሲሆን አንድ ጋዜጠኛ በሞባይሉ ያነሳውን ፎቶ እንዲያጠፋ ተደርጐ ተለቀናል፡፡ ፖሊስ ጣቢያው ውስጥ የነበሩ ከ70 በላይ ሰዎች ማተሚያ ቤት እስክንገባ ድረስ በእስር ላይ እንደነበሩ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
Soorce: http://www.addisadmassnews.com

ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 16, 2013

የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት እርማጃና ተቃዉሞዉ

Geez Bet | Saturday, November 16, 2013
አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል። 
  መንግስት ፈቃድ እንዳልተሰጠዉ በማመልከት ቁጥራቸዉን ባይጠቅስም የታሰሩ መኖራቸዉን ገልጿል። ሰልፉን ያስተባበረዉ የተቃዉሞ ወገን ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ ሁለት ሊቃነመናብርቱን ጨምሮ አንድ መቶ ሰዎች ገደማ መያዛቸዉን አመልክቷል። የመንግስት ቃል አቀባይ አቶ ሽመልስ ከማል ፀረ አረብ ስሜት ሊፈጥር የሞከረ ያሉት ተቃዉሞ ሰልፍ አዘጋጆች ከሚመለከተዉ አካል ፈቃድ ባለማግኘታቸዉ እንደሚከሰሱ ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ገልጸዋል። በፖሊስ ከተደበደቡት አንዱ እንደሆነ የገለጸዉ፤ አስፋዉ ሚካኤል መንግስት የሳዉዲ አረቢያን ድርጊት ላይ የቀረበዉን ተቃዉሞ ለምን ማገድ እንደፈለገ እንዳልገባዉ ለዜና ወኪሉ ገልጿል።
ዘገባዉ አክሎም ፖሊስ አንዳንድ ጋዜጠኞች ያነሱትን ፎቶግራፍ መደምሰሱንም አመልክቷል። የመንግስት ቃል አቀባይን አስተያየት ማግኘት እንዳልተቻለም ተገልጿል። ለተለያየ ሥራ ሳዑድ አረቢያ የሚገኙ የዉጭ ዜጎች ሕጋዊ መኖሪያ ፈቃድ እንዲያወጡ የተሰጠዉ የጊዜ ገደብ ካለቀ ወዲህ እዚያ ያሉ ኢትዮጵያዉያን ጥቃት እየደረሰባቸዉ እንደሚገኝ እየገለፁ ነዉ።
የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም፥ በኢትዮጵያዉያን ላይ የሚፈፀመዉን በደል በመቃወም ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘዉ የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ አደባባይ ወጥተዉ ነበር።ይሁንና የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር የጠቀሰዉ ጋዜጠኛ እንዳለዉ ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ በኢትዮጵያዉያን ላይ የተፈፀመዉ አዲስ አበባም ተደገመ።
የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት በሐገሩ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉን ላይ የሚያደርሠዉን በደል፥ በተለያዩ ሐገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአደባባይ ሠልፍ እያወገዙት ነዉ።ትናንት እዚሕ ጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ፍራንክፈርት ዉስጥ ባደረጉት ሠልፍ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ኢትዮጵያዉያኑን፥ ማንገላታት፥ ማሠር፥ መደብደብ መግደሉን እንዲያቆም፥ የኢትዮጵያ መንግሥትም የዜጎቹን መብት እንዲያስከብር ጠይቀዉ ነበር።የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም፥ በኢትዮጵያዉያን ላይ የሚፈፀመዉን በደል በመቃወም ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘዉ የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ አደባባይ ወጥተዉ ነበር።
ይሁንና የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር የጠቀሰዉ ጋዜጠኛ እንዳለዉ ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ በኢትዮጵያዉያን ላይ የተፈፀመዉ አዲስ አበባም ተደገመ።ሠልፈኞቹ ተቃዉሟቸዉን ለማሰማት ገና ከመሠብሰባቸዉ ፖሊስ ደብድቦ አብዛኞቹን በተነ፥ የተቀሩትን አሠረ።ዮሐንስ አጭር ዘገባ ልኮልናል።
ዩናይትድ ስቴትስ ርዕሠ-ከተማ ዋሽግተን-ዲሲ እና አካባቢዋ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያዉያንም የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት በኢትዮጵያዉያን ላይ የሚወስደዉን እርምጃ በአደባባይ ሠልፍ አዉግዘዋል። የዋሽግተኑ ወኪላችን አበበ ፈለቀ እንደዘገበዉ ትናንት የተጀመረዉ የአደባባይ ሠልፍና ዉግዘት በተለያዩ የሰሜን አሜሪካ ከተሞችም ይቀጥላል።
የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት ኢትዮጵያዉያንን ጨምሮ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚኖሩ የዉጪ ሐገር ዜጎችን ከሐገሩ ማባረሩን ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ። የጂዳዉ ወኪላችን ነብዩ ሲራክ እንደነገረን በኢትዮጵያዉያንና በሳዑዲ አረቢያ ዜጎች መካካል ሰሞኑን ተከስቶ የነበረዉ ደም አፋሳሽ ግጭት ዛሬም ጋብ ብሏል።ከዚሕ ቀደም ኮንትራታቸዉ ተቋርጦ፥ ቀጣሪዎቻቸዉ ጠፍተዉ፥ ወይም ታመዉ ጂዳ ኢትዮጵያ ቆንስላ ዉስጥ ለወራት ተጠልለዉ የነበሩ ኢትዮጵያዉያንም ወደ ሐገራቸዉ ለመመለስ ማቆያ ጣቢያ ገብተዋል። ነብዩን ከአንድ ሠዓት በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ። የመጀመሪያዉ ጥያቄዬ ምን አዲስ ነገር ---የሚል ነበር።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር/ አበበ ፈለቀ
ነብዩ ሲራክ/ ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ
Source: www.dw.de
 
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 14, 2013

በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያውያን ስቃይ

Geez Bet | Thursday, November 14, 2013

በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያውያን ስቃይ

ሳዉድ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ዛሬም የድረሱልን ድምጻቸዉን እያሰሙ ነዉ። የሀገሪቱ መንግስት ላለፉት ወራት ሰጥቶ የቆየዉ የምህረት ቀነገደብ ካለፈ ወዲህ በዜጎችና የጸጥታ ኃይሎች ይፈጸምብናል የሚሉት በደልም ገደብ ማለፉን ይናገራሉ።
በሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ከ24ዓመታት በላይ እዚያ እንደኖሩ ለዶቼ ቬለ የገለጹት አንድ ዜጋ ደግሞ ኢትዮጵያዉያኑ ላይ ሀገሬ የሚያሳየዉ ጥላቻ ዛሬ አልተጀመረም ባይናቸዉ። ከያሉበት ታፍሰዉ በመጠለያ ስፍራ እንደተሰበሰቡ ያመለከቱ ወገኖች ደግሞ ኤምባሲዉ አልደረሰልንም፤ ካለንበት የሚያወጣን አጣን ይላሉ።

ከእነልጆቻቸዉ ታፍሰዉ መጠለያ ከተከተቱ እናቶች አንዷ ናቸዉ። እንባቸዉን እየታገሉ የሚሉት አንድ ነገር ነዉ፤ ድሃም ብትሆን ሀገር አለን። ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት በርካቶች በአዉቶብስ ያለ ሕጋዊ መኖሪያ ፈቃድ ሀገሪቱ ዉስጥ የተገኙትን የተለያዩ ሀገር ዜጎች በመሰብሰብ ወደመጠለያ ስፍራ ያጓጉዛሉ። በስልክ ያነጋገርኳቸዉ ኢትዮጵያዉያን የት ቦታ እንዳሉ ማወቅ እንደተሳናቸዉ ቢናገሩም ወንዶችና ሴቶችን ለየብቻ ተደርገዉ በመጠለያ መታጎራቸዉን ገልጸዉልኛል። ሴቶቹ ሶስት ሺህ እንሞላለን ባዮች ናቸዉ። ይህንም በአንድ አካባቢ ብቻ መሆኑ ነዉ። እዚህ ቦታ ካሉት አንዷ እሷ ብቻ ሳትሆን ሌሎችም በተሰባሰቡበት መጠለያ ስፍራ ባለዉ መጥፎ ሽታ ምክንያት ድምፃቸዉ መዘጋቱን ለበሽታም መዳረጋቸዉን ገልጻልኛለች። ወንዶች ትላለች ወጣቷ ከአረብ ወጣቶች ጋ ጸብ ዉስጥ ገብተዋል። እንደእሷ ገለጻም ሸባቦቹ ግራ የተጋቡትን ኢትዮጵያን ሴቶች ባገኙበት አስገድደዉ ይደፍራሉ፤ ከመጠለያዉም አፍነዉ ይወስዳሉ።
ወደሳዉዲ ከተሻገረ ብዙም ወራት እንዳልሆነዉ የገለፀልኝ ከስልጤ ነዉ የመጣሁት ያለኝ ሽፋ ሸምሱ ደግሞ ወደሀገሩ ለመመለስ ተዘጋጅቷል፤ ግን ወደአዉሮፕላን ማረፊያ ይወስዳችኋል የተባለዉን አዉቶብስ መጠበቅ ቀጥሏል የተባለዉ ግን የለም ይላል።
ሳዉዲ ዉስጥ ኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በርካታ የዉጭ ዜጎች በሠራተኝነት ይገኛሉ። መንግስት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ለሌላቸዉ በሰጠዉ የምህረት ጊዜ የተጠቀሙ የባንግላዴሽ፤ ፊሊፒንስ፤ ህንድ፤ ኔፓል፤ ፓኪስታንና የመን ዜጎች ቁጥር በርካታ መሆኑን ዘገባዎች ያመለክታሉ። እንደአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ዘገባ ከሆነም ወደአንድ ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑ ተጠሪ የሚሆኗቸዉ ቀጣሪዎች አግኝተዋል። ዘጋቢዎች ያነጋገሯቸዉ ኢትዮጵያን ግን ለዓመታት ያፈሩትን ንብረት በርካሽ ለመሸጥ ተገደዋል ገሚሱንም ለሰዎች ሰጥተዋል። በእጅ የቋጠሯትን ገንዘብም መኖሪያ ፈቃድ ለማስተካከል በደላልነት ለቀረቧቸዉ የሳዉዲ ብልጣብልጦች አጉርሰዋል። ተስፋ ያደረጉትን ግን አላገኙም።
በሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪቃዉያን ስደተኞች በሳዉዲ መንግስት ኃይሎች ታስሰዉ ቢያዙም የኃይል ጥቃቱ የበረታዉ ኢትዮጵያዉያኑ ላይ ነዉ ይላሉ እዚያ የሚገኙት ወገኖች።
ሳዉዲ የሚገኙ ወገኖች ዛሬም ኤምባሲዉ ላይ የሚያቀርቡት ቅሬታና ለመንግስትም የሚያቀርቡትን አቤቱታ በማስመልከት ከዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምላሽ ለማግኘት ያደረግነዉ ተደጋጋሚ ሙከራ ባለመሳካቱ የባለስልጣናቱን ሃሳብ ማካተት አልቻልንም።
ከሃገሪቱ መውጣት ያልቻሉ ዜጎች በዋና ከተማይቱ በሪያድና በሌሎችም ከተሞች በጎዳናዎች ላይ እየወጡ መንግሥት በአስቸኳይ ወደ ሃገራችው እንዲልካቸው ሲጠይቁ ከየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ጋር መጋጨታቸውን የጂዳው ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ዘግቧል ።
በርካታ ኢትዮጵያውያን ዛሬም ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በመሰቃየት ላይ መሆናቸውን እየተናገሩ ነው ። እነዚሁ ከሃገሪቱ መውጣት ያልቻሉ ዜጎች በዋና ከተማይቱ በሪያድና በሌሎችም ከተሞች በጎዳናዎች ላይ እየወጡ መንግሥት በአስቸኳይ ወደ ሃገራችው እንዲልካቸው ሲጠይቁ ከየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ጋር መጋጨታቸውን የጂዳው ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ዘግቧል ። ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ያለህጋዊ የስራና የመኖሪያ ፈቃድ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች ህጋዊ ሰነድ እንዲያወጡ አለያም ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ መንግሥት የሰጠው የምህረት ቀነ ገደብ ካበቃ ዛሬ 10ኛ ቀኑን ይዟል ። በነዚህ 10 ቀናት ውስጥ ወደ 23 ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ለሳውዲ መንግሥት እጃቸውን መስጠታቸው ተዘግቧል ። የጂዳውን ወኪላችንን ነበዩ ሲራክን ስለ አጠቃላዩ ሁኔታ በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።

ሸዋዬ ለገሠ / ነበዩ ሲራክ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ

Source: www.dw.de
ሙሉውን አንብብ-Read More

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በIMF እይታ

Geez Bet | Thursday, November 14, 2013
የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ኣስመልክቶ ላለፉት 9 እና 10 ዓመታት በተለይ ከመንግስት በኩል የሚሰማው እጥፍ ድርብ እድገት ወይንም በእንግሊዝኛው Double digit grorth ያውም ከ 11 በመቶ ያላነሰ ወይንም ከዚያ በላይ መሆኑ ይታወቃል። ተቃዋሚዎች በዚያች ኣገር ያንን ያህል እድገት ያውም በኢህኣዲግ የእጅ ኣዙር እዝ ኢኮኖሚ የማይታሰብ ነው እያሉ

ማጣጣላቸው ባይቀርም የዓለም ባንክ እና ዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ተቐም IMF ግን ሙሉ በሙሉም ባይሆን የመንግስትን የዕድገት ብስራት የሚጋሩት ይመስላል። የመንግስት ባለስልጣናት ለተባለው እድገት በየዘርፉ እና በየአካባቢው እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ ልማት ኣውታሮቶችን እና የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ መሻሻሉን እንደ ማስረጃ ሲያቀርቡ ተቃዋሚዎች እና ኣንዳንድ ገለልተኛ የሆኑ ባለሙያዎችም እንዲሁ ከወረቀት ኣልፉ መሬት ላይ ያረፈ እና የህብረተሰቡን ኑሮ የቀየረ እድገት ኣላታየም ሲሉ በተቃራኒው ይከራከራሉ። የዓለም ባንክ እና ዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ተቐም IMF በበኩላቸው በኢትዮጵያ መጋነኑ ባይቀርም ነገር ግን ፈጣን እድገት መኖሩን እና በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ደግሞ የህዝቡ ኑሮም እየተቀየረ መሆኑን ይመሰክራሉ።
የተለመደው የኢኮኖሚ እድገት መለኪያ ባለሙያዎችም እንሚሉት ኣጠቃላይ የኣገር ውስጥ ገቢ እና ምርት ዕድገት ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስትም በአብዛኛው በዓማካኝ 11 በመቶ ለተባለው ዓመታዊ ዕድገት ዋንኛ መሰረቱ የግብርና ምርት እድገት መሆኑን ሲገልጽ ቆይቷል። ይሁን እንጂ የውጪው እርዳታ እና ብድር ግብዓቶችም ሆኑ የውጪ ምንዛሬውም የሚኖራቸው ድርሻ ቀላል ኣለመሆኑን መገመት ይቻላል።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት በሚመጣውም ዓመት በተመሳሳይ መልኩ ሊቀጥል እንደሚችል የገመተው ዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ተቐም IMF ባለፈው ወር ይፋ ባደረገው ዓመታዊ ሪፖቱ ይህንኑ ጠቁሟል። መንግስታዊ ለሆኑ የልማት ተቐማት የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ ክፍተት ካሳየ እና የውጪ ምንዛሪ እጥረት ካጋጠመ ግን የተባለው እድገት ላይሳካ እንደሚችል IMF ኣልሸሸገም።
በቀጣዮቹ 12 ወራት የኣገሪቱ ኣጠቃላይ የኣገር ውስጥ ምርት በዓማካኝ የ 7 በመቶ እድገት ይኖረዋል የሚለው IMF ይህ ግን የፖሊሲ ማስተካከያ ካልታከለበት ኣንድ ቦታ ላይ መቆሙ ኣይቀሬ ነው ሲልም ያስጠነቅቃል።
መንግስት መር የኢኮኖሚ ልማት ፖሊሲን የሚከተለው የኢትዮጵያ መንግስት ይላል IMF እንደ ዓባይ ግድብ የመሳሰሉ ግዙፍ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በራሱ ዓቅም ለማካሄድ ወስኖ ጀምሮታል። ይህ ፕሮጀክት የ 80 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን በሪፖርቱ መሰረት 10 በመቶ የሚሆነውን የኣገሪቱን ዓመታዊ የኣገር ውስጥ ገቢ መጠን ይወስዳል ማለት ነው። እናም እድገቱ በዚህ ምክኒያት እንዳይሰናከል እና ቀጣይነት እንዲኖረው ለማድረግ ከተፈለገ መንግስት የግል ባለሀብቶች በላቀ ደረጃ በኢንቨስትመንቱ ውስጥ እንዲሳተፉ በር ሊከፍትላቸው ይገባል ሲል IMF ይመክራል።
የኣገር ውስጡ የልማት እንቅስቃሴ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ግብዓትን ይጠይቃል። የገንዘብ ኣቅርቦቱ ግን መሰናክል የሞላበት ነው ሲልም IMF ይወቅሳል። ለዓብነት ያህልም የግል ባንኮች እንቅስቃሴ ኣለመበረታታቱ እና የመnንግስት ባንኮችም ቢሆኑ ለግሉ ዘርፍ የሚሰጡት ብድር በቂ ኣለመሆኑን IMF ይጠቅሳል። ያለ ግል ባለ ሀብቶች ንቁ ተሳትፎ ግን የተጀመረው የኢኮኖሚ እድገት ቀጣይ ሊሆን እንደማይችል ሊሰመርበት ይገባል ሲል ሪፖርቱ ይቀጥላል።
የሆነ ሆኖ ይላል ዘገባው እ ኣ ዘ ኣ ከ 2001 እና 2002 ጀምሮ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዓማካኝ በዓመት በ 7 በመቶ እድገት ኣሳይቷል። ይህም ይላል ዘገባው በዚያች ኣገር የድህነት እርከኑን በግማሽ ቀንሶታል። ይህ ማለት በሪፖርቱ መሰረት በ 2005 60,5 የነበረው የድህነት እርከን በ 2012 ወደ 30,7 ወርዷል። ይህም የበርካቶችን ኑሮ ኣሻሽሎታል የስራ ኣጥ ቁጥርንም በእጅጉ ቀንሶታል ያለው IMF በዚህ መካከል ግን የመንግስት በተለይም የገዢው ፓርቲ ኩባንያዎች በኣገር ውስጥ የገንዘብ ኣቅርቦት ተጠቃሚ ሲሆኑ የግል ተበሪዎች ግን ገለል መደረጋቸውን ሳይጠቅስ ኣላለፈም።
2012/13 7 በመቶ የተመዘገበው እድገት በዋናነት ከግብርና ከኮንስትራክሺን እና የኣገልግሎት ዘርፎች የተገኘ መሆኑን የጠቀሰው IMF ከዚሁ የተነሳ በ 2011 40 በመቶ ደርሶ የነበረው የዋጋ ግሽበትም በ 7 በመቶ መቀነሱን ጠቅሶ ነገር ግን በ 2012 2,8 ቢሊዮን የነበረው የበጀት እጥረት በ2013 ወደ 3 ቢሊዮን ከፍ ማለቱንም በሪፒርቱ ኣመልክቷል።

በኣፍሪካ ዋናዋ የቡና ኣምራች የሆነችው ኢትዮጵያ የብድር እና እዳ ይዞታዋን በሰከነ መልኩ ለማስኬድ ያስችላት ዘንድ IMF እንደሚለው የፋይናንስ ስርዓቷን ማሻሻል ይኖርባታል። በተለይ የግል ባንኮች በብድር ባሰራጩት ገንዘብ መጠን 27 በመቶ ያህል የመንግስት ሰነድ ሽያጭ እንዲገዙ የሚያስገድደውን ደንቃራ ደንብ ማስወገድ እንደሚኖርባት ኣመልክቷል።
ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ለዓመታት ያህል በስሌቱ ላይ ስምምነት ኣልነበረንም የሚሉት በአዲስ ኣበባ የIMF ተጠሪ ሚ/ር ጃን ሚኬልሰን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት መጠነኛ ማሻሻያ ማድረጉን ይናገራሉ።
የኢኮኖሚ ባለሙያው እና በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ግን የ IMF ዘገባ በመንግስት መረጃዎች ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ችግር ያለበት ነው ይላሉ።
መረጃዎችን ከመንግስት እንደሚቀበሉ ያልሸሸጉት የ IMF ተወካይ ሚ/ር ጃን ሚኬልሰን ነገር ግን በራሳችን ስልት እንመዝናቿለን ይላሉ።
የኣንድነት ለዲሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ ም/ሊቀመንበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ በበኩላቸው የIMF መመዘኛ በተዛቡ የመንግስት መረጃዎች ላይ እስከተመሰረተ ድረስ ትርጉም ኣይኖረውም ሲሉ በደርግ ጊዜ የታዘቡትን ተመሳሳይ የእድገት መለኪያ ያስታውሳሉ።ምንም እንኩዋን መንግስት በሚያስተዋውቀው ደረጃ ባይሆንም የተጠቀሰው እድገት ህብረተሰቡን በስፋት እየጠቀመ መሆኑን IMF ያምናል ይላሉ ሚ/ር ሚኬልሰን
አቶ ግርማ ሰይፉ ግን ይህንን ኣይቀበሉትም በኣጠቃላይ ግን የኢትዮጵያ መንግስት ኣንድ ነገር ካላደረገ በስተቀር የኣገሪቱ እድገት ኣሁን ኣንድ ሊያልፈው ከማይችል ፈታኝ ደረጃ ላይ ደርሷል ይላሉ በአዲስ ኣበባ የIMF ተጠሪ ሚ/ር ጃን ሚኬልሰን።
ጃፈር ዓሊ
አርያም ተክሌ
Source: www.dw.de
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 13, 2013

Gangrene/ጋንግሪን፡ በደም እጥረት የሞተ የሰውነት ክፍል

Geez Bet | Wednesday, November 13, 2013

ሕመም የትኛውም አካል ላይ ሲከሰት ያሰቃያል። የሕመም ትንሽ የለውም። ይሁንና አንዳንዴ ሕመምን ከሕመም የማበላለጥ ሃሳብ ይሰጣል። «እንደ ጣት ቁስል አትነ ዝንዘኝ» የሚለው የጣት ቁስለትን ጥዝጣዜ ያመለክታል። ይህን የጠቀስኩት ብዙውን ጊዜ ከእግር ጣትና እጅ ላይ የሚከሰተውን ሕመም ምንነት መከላከያና ሕክምና ወዘተ የተመለከቱ መረጃዎችን ለመስጠት አስቤ ነው። – ስለ «ጋንግሪን። ስለ ጋንግሪን ማብራሪያ የሰጡን ዶክተር ሄለን ይፍጠር ይባላሉ። 
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔ ሻሊስት ሐኪምና በስኳር ሕመም ትምህርትና ጥናት ላይ የሚገኙ ምሁር ናቸው።
ጥያቄ፡- ጋንግሪን ምንድን ነው?
ዶክተር ሄለን፡- ጋንግሪን ወደ አማርኛ ሲመለስ በደም እጥረት የሞተ የሰውነት ክፍል እንደማለት ነው። አንድ የሰውነት ክፍል ደም አጥሮት ምግብና ኦክስጅን አልደርሰው ብሎ ሲጠቁር ሕይወት አልባ ሆኖ ሲሞት ጋንግሪን ተፈጥሯል ማለት ነው።
ጥያቄ፡- የጋንግሪን መነሻ ወይም መከሰቻ ምክንያቶች ምን ምን ናቸው?
ዶክተር ሄለን፡- አንደኛ በተለያዩ አደጋዎችና ምክንያቶች የደም ዝውውር ቢቋረጥ ያ ዝውውሩ የተቋረጠበት የሰውነት ክፍል ጋንግሪን ይፈጥራል። ሁለተኛ የልብ ችግር ያለባቸው ሰዎች ደም ይረጋና ከልብ ወደ ደም ሥሮች ይሄዳል። ትንሽም የረጋች ደም ብትሄድ መተላለፊያ ትዘጋለች። ይህች የረጋች ደም የዘጋችው የደም ሥር ይመግበው የነበረው የአካል ክፍል ጋንግሪን ይፈጥራል። በደም ምግብና አየር እጥረት ምክንያት ይሞታል።ሦስተኛ በደም ሥር ጥበት ጋንግሪን ይፈጠራል። በረጅም ጊዜ የመጣ የስኳር ሕመምተኞች፣ የደም ግፊት ችግር ያለባቸውና የደም ቅባት ከፍ ያለባቸው ሕሙማን የደም ሥራቸው ሊጠብ ይችላል። ደም ሥራቸው ላይ ቅባት እየተጋገረ ጠቦ በመጨረሻ የደም መተላለፊያ ይዘጋል። ደም ከተቋረጠበት አካል በታች ያለው ሰውነት ጋንግሪን ይፈጠርበታል። አራተኛው ምክንያት ኢንፌክሽን ነው። የሰውነት ክፍል ኢንፌክሽን ፈጥሮ ሲያብጥበትና በባክቴሪያ ሲጠቃ በደም ሥር ደም አይደርሰውም። የምግብ ዑደቱ ስለሚቋረጥ ጋንግሪን ይፈጠራል ይሞታል።
ጥያቄ፡-የጋንግሪን ሕመም በዘር ይተላለፋል?
ዶክተር ሄለን።- በተወሰኑ የደም ስር ችግሮች (እንደ ስኳር ባሉ) በዘር የሚመጣ ችግር በጣም አነስተኛ ነው። ነገር ግን ስኳር ሕመም ሳይኖርም በማጨስና በሌላም ምክንያት የደም ዝውውርን መዝጋት ጋንግሪን ሊያመጣ ይችላል። ዋና መነሻዎች የሚባሉት ረዥም ዓመት የቆየ የደም ግፊት፣ የስኳርና የደም ቅባት (ኮሌስትሮል) ችግሮች የደም ሥር ጥበትና መዘጋት ናቸው።
ጥያቄ፡- ጋንግሪን በአገራችን ምን ያህል ችግር እያደረሰ ነው?
ዶክተር ሄለን፡- የጋንግሪን ሕመም የሚከሰትባቸው ሰዎች ከሃምሳ ከመቶ በላይ የስኳር ሕመም ያለባቸውና በስኳር ሕመም መያዛቸውን የማያውቁ ናቸው። የእግር ቁስለት ያጋጠማቸውና በጋንግሪን የታመሙ ሲመረመሩ ስኳር ሕመምተኛ ሆነው ይገኛሉ። የዓይንና የነርቭ ችግር አጋጥሟቸው ሲመረመሩም ስኳር ሕሙማን ሆነው
ይገኛሉ።በዓለም አቀፍ ደረጃ ከስኳር ሕሙማን ከአሥራ አራት እስከ ሃያ አራት ከመቶ ቢያንስ አንድ ጊዜ የእግር ቁስለት ያጋጥ ማቸዋል። ከእነዚህም ሃያ አምስት ከመቶው በቁስለቱ ምክንያት የእግር መቆረጥ ያጋጥማቸዋል። በአገራችንም ከሕክምና ክትትልና ስኳርን ከመቆጣጠር ባህል እንዲሁም ስኳርንና የእግር ቁስለትንም ሆነ ጋንግሪንን ቀድሞ ከመከላከል ዝቅተኛነት የተነሳ እርግጡን መናገር ባይቻልም ከዓለም አቀፉ ተሞክሮ እንደ ሚበልጥ ይገመ ታል። በጥናት ባይሆንም በየቀኑ የሚታየው ይህ ነው። በአገራችን ምልክት የማያሳየው 2ኛው ዓይነት ከሰላሳና አርባ ዓመት በኋላ የሚከሰተው የስኳር ሕመም እየተስፋፋ ነው። የእግር ቁስለትና የጋንግሪን በሽታም በዚያው መጠን የሕሙማኑን ጉዳት እያባባሰ ነው።
ጥያቄ፡- የጋንግሪን በሽታ መከላከያ ምንድን ነው?
ዶክተር ሄለን፡- ዋናው መከላከያው የስኳርን ሕመም መኖር አለመኖር ቀድሞ ተመርምሮ ማወቅ ነው። 2ኛው ዓይነት የስኳር ሕመም (ከጉልምስና ዕድሜ ጀምሮ የሚከሰት) ምልክት የለውም። በቅድሚያ መመርመር። የደም ግፊት ካለም ቀድሞ መመርመር። የሚያጨሱ የልብ ችግር ያለባቸው ክብደታቸው ከፍ ያለና በዘር የስኳርና የግፊት ችግር ያለባቸው ቀድመው መመርመር አለባቸው። ስኳር ከተገኘ ሕክምናውን በሚገባ መከታተል፣ ግፊትና የደም ቅባትን መቆጣጠር፣ ማጨስን ማቆም፣ ለእግር ጥንቃቄ ማድረግ ጋንገሪንን ቀድሞ መከላከል ነው።
ጥያቄ፡- የጋንግሪን ሕመም ሕክምናው ምንድን ነው?
ዶክተር ሄለን፡- ጋንግሪን የሞተ የአካል ክፍል ላይ የሚከሰት በመሆኑ መወገድ ብቻ ነው ሕክምናው። እጅና እግር ላይ የሞተ አካል ዝም ከተባለ ይስፋፋል። ወደ ሌሎች አካባቢዎች ይሠራጫል። ለከፍተኛ ሕመምና ሞት ይዳርጋል። በምግብና ኦክስጅን እጥረት የሞተ አካል በመሆኑ ማስቀጠል አይቻልም። እንዳይፈጠር መከላከል
እንጂ ጋንግሪን ከተፈጠረ ያ የተፈጠረበት አካል ሕይወት አልባ ስለሆነ የትም አገር ቢኬድ ተቆርጦ ነው የሚወጣው።
ጥያቄ፡- ጋንግሪን በእግርና በእጅ ላይ ብቻ ነው የሚከሰ ተው?
ዶክተር ሄለን፡- ብዙውን ጊዜ በእግርና እጅም ላይ ይከሰታል። እጅና እግር ላይ የሚወጣው ነው «ጋንግሪን» የተባለው። ሆኖም በሌላ የሰውነት አካልም የደም ዝውውር ቢቋረጥ ጋንግሪን ሊፈጠር ይችላል።
ጥያቄ፡- ብዙ ጊዜ በእግር ላይ የሚከሰት ከሆነ ለእግር የተለየ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈ ልጋል?
ዶክተር ሄለን፡- አዎ! ለእግር የተለየ ጥንቃቄ ያስፈልጋል። የነርቭ ችግር የደም ሥር ጥበት ከተከሰተና የስኳር ሕመም ካለ በየቀኑ እግርን ማየት በዓመት አንድ ጊዜ እግርን መመርመር ያሻል። « የደም ዝውውሩ ጥሩ ነው አይደለም በእግሩ ላይ ያለ ስሜት ቀንሷል? የእግር ቅርጽ ለውጥ አለ?» የሚሉት ይመረመራሉ። ቁስል የነበረበት ከሆነም መታወቅ አለበት። ከእነዚህ አንዱ ችግር ካለ ለቁስለትና ለመቆረጥ እንዳይ ጋለጥ መከላከል ይገባል። ግለሰቡ በየቀኑ እግሩን ማየት አለበት። በላይ፣ በታች ፣በጣቶቹ መሐል ስሜት መኖሩን ለውጥ መከሰቱን ልብ ማለት አለበት። በየቀኑ ማታ መታጠብ ማድረቅና ደርቆ ተሰነጣጥቆ ኢንፌክሽን እንዳይፈጠር እንደሎሽን ያሉ ቅባቶችን መቀባት ይመከራል፡፡ ጥፍሩን ሲቆርጥ በምላጭ በሰንጢ ሳይሆን በጥፍር መቁረጫ መሆን አለበት፡፡ አቆራረጡ በቀጥታ (አግድም) ነው፡፡ ጎንና ጎኑን በሞረድ ማስተካከል ይበቃል። ይህ አቆራረጥ ለሁሉም ሰው ጥሩ ነው።
ሌላው ጥንቃቄ የጫማና ካልሲ ነው። ስልሳ ከመቶው የእግር ቁስለት በስኳር ሕሙማን ላይ የሚከሰተው ከጫማ ጋር በተያያዘ ነው። አዲስ ጫማ ይጠባል፤ ብዙ ይኬድበታል፤ እግር ይላጣል ፤ ውሃ ቋጥሮ ችግሩ ይጀምራል። ጫማ ማሠሪያ ያለው፣ ጫፉ ሹል ያልሆነና ብዙ ሙቀት የማይፈጥርና የሚመች መሆን አለበት።
ሴቶች ባለተረከዝ ጫማና ክፍት ጫማ ለአደጋ ስለሚያጋልጣቸው መተው አለባቸው። በቤትና በየትኛውም ቦታ በባዶ እግር መሄድ ክልክል ነው። ካልሲም የጥጥና ጫፉ ተቀዶ ጣትን ለጫማ ፍትጊያ የማያጋልጥ መሆን አለበት።
ጥያቄ፡- ጥፍርን ገባ ብሎ መቁረጥ ለጋንግሪን እንደሚያጋልጥ የሚነገረው እውነት ነውን?
ዶክተር ሄለን፡- ጥፍርን በመቆረጥ ብቻ ጋንግሪን ሊመጣ ይችላል ማለት አይደለም። የእግርና የእጅ መቁሰል ወደ ጋንግሪን የሚሄደው አስቀድሞ የስኳር፣ የደም ስር ጥበትና መሰል የጤና ችግር ነው። በሽታ የመከላከል አቅማቸው ከሌላው ያነሰ ነውና በትንሽ ክፍተት ኢንፌክሽን ይፈጥርና ባክቴሪያ ይይዝና ቶሎና በቀላሉ
የማይድን እብጠት ይፈጠራል። በተለይ የስኳር ሕሙማን ከጥፍሩ ጋር የተያያዘውን ሥጋ ከነኩ በቀላሉ ለችግሩ ይጋለጣሉ።
ጥያቄ፡- የእግር ቁስለት ወደ ጋንግሪን ተቀይሮ ሙት ወይም ሕይወት አልባ የሆነበት ሰው ጣቱ ወይም እግሩ መቆረጥ እንዳለበት ሲነገረው ምን ይመልሳል?
ዶክተር ሄለን፡- ሰውኛ ነው። ማንም ሰው አካሉን ማጣት አይፈልግም። ማንም ሰው ቶሎ አይቀበለውም። በጣም የታመመ ወይም ሕይወቱ አደጋ ላይ የሆነ ካልሆነ በቀር ወዲያው አይስማማም። « የሚሆን ነገር ሞክሩልኝ እንጂ!» ይላል።
ጥያቄ፡- ውሳኔያችሁን አልቀበል ብሎ የሚሄድ አለ?
ዶክተር ሄለን፡- እንቢ ብሎ በጊዜ ሳይስፋፋ ይቆረጥ ተብሎ ጥሎ ሂዶ ብሶበት የሚመጣ አለ። አማራጭ ሲያጣ ነው የሚስማማው። እኛ ግን ቆስሎ ጠቁሮ ከሞተ መመለስ አይቻልም። ሌላ ሕክምና የለውም ብለን እናስረዳለን።
ጥያቄ፡- የአሁኑ መልዕክትዎ ምንድን ነው?
ዶክተር ሄለን፡- ቀድሞ መከላከል። ስኳርን መመርመር፤ ቁስለት ከተከሰተ በባለሙያ መታከም ነው። የደም ስር ጥበትንና የሚሞት አካልን በሌላ ደም ስር ደም እንዲያገኝ የሚያደርጉ አዳዲስ ሕክምናዎች አሉ። ቁስለት ሲኖር በቅባት፤ በሎሚ… ከማለት ቀድሞ መታከም ይገባል። ቁስለቱ ተባብሶ ሆስፒታል እስከሚተኙ መጠበቅ
ችግሩን ያበዛዋል።
ጥያቄ፡- አመሰግናለሁ!
ዶክተር ሄለን ፡- እኔም አመሰግናለሁ! 
Source: www.tenaadam.com

ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 11, 2013

የስዑዲ ምህረትና የሁለት ኢትዮጵያውያን መገደል

Geez Bet | Monday, November 11, 2013
የሳውዲ መንግሥት ለ ሁለተኛ ጊዜ የሰጠው የምህረት አዋጅ ቀነ ገደብ ካበቃበት ካለፈው እሁድ አንስቶ በተካሄደ የፖሊስ ክትትል ሁለት ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን ሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አስታወቁ ። እነዚሁ ነዋሪዎች እንዳሉት ባለፉት ሶስት ቀናት ከሞቱት ሌላ በርካታ ኢትዮጵያውያን ታፍሰዋል ።
በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ከሞላ ጎደል ሥራቸውን አቁመዋል። የጅዳው ወኪላችን ነበዩ ሲራክ እንደዘገበው የምህረቱ የመጨረሻ ቀን ካለፈ በኋላ መንግስት በወሰደው እርምጃ ከ 5 ሺህ በላይ የተለያዩ ሃገራት ዜጎች ተይዘዋል። መንግሥት ሕገወጥ የሚላቸው እነዚህ የውጭ ዜጎች የሁለት ዓመት እሥራትና 100 ሺህ የሳውዲ ሪያል ቅጣት ይጠብቃቸዋል። ከምህረት አዋጁ ማለቅ በኋላ በጂዳ የኢትዮጵያውያን ዓለም ዓቀፍ ትምህርት ቤት ሥራ መስተጓጎሉንም ነብዩ ሲራክ ከጅዳ ዘግቧል ።

ነብዩ ሲራክ
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ
Source: www.dw.de
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 5, 2013

አነጋጋሪዉ የስለላ ቅሌትና ጀርመን

Geez Bet | Tuesday, November 05, 2013
የአሜሪካንን ምስጢራዊ መረጃዎች ያጋለጠው የቀድሞው የአሜሪካን የስለላ ድርጅት ባልደረባ ኤድዋርድ ስኖውደን፤ ባለፈዉ ሳምንት ሐሙስ ከታዋቂዉ የጀርመን ፖለቲከኛ ጋር ሞስኮ ላይ ሲገኛኝ ጀርመን ሁኔታዎችን ካመቻቸችለት በጀርመን ምክር ቤት ተገኝቶ ስለ አሜሪካ የስለላ ጉዳይ በግልፅ ለመናገር እንደሚፈልግ መናገሩ ይታወቃል።
       ይህ ከተሰማ ከቀናቶች በኋላ ደግሞ የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ አርቃቂዎች ለቀድሞዉ የአሜሪካ የስለላድርጅት ባልደረባ ለኤድዋርድ ስኖዉደን ምንም ዓይነት ምሕረት እንደማይሰጡ ተናግረዋል። የስኖዉደን እና የአሜሪካ ዛቻ የጀርመናዉያን ለስኖዉደን ጥገኝነት ለመስጠት መፈለግ እያነጋገረ መሆኑን የዶቼ ቬለዉ ፍሪደል ታዉበ ዘግቧል። የአሜሪካንን ምስጢራዊ መረጃዎች ያጋለጠው የቀድሞው የአሜሪካን የስለላ ድርጅት ባልደረባ ኤድዋርድ ስኖውደን፤ የስደት ህይወት ፀጥታ የነገሰበት አይደለም። ስኖዉደን ከቤተስብ እና ጓደኛ ናፍቆት ባሻገር፤ ሌሎች ጥቃቅን ነገሮችን ሁሉ እንደሚናፍቅ ተናግሮአል። ከነዚህ መካከል ደግሞ በአሜሪካ በፍቅር ይበላዉ የነበረዉ እስካሁን ግን በሩስያ ያላገኘዉ ደረቅ የድንች ጥብስ መሰል ምግብ በዐይኑ ላይ መዞሩ ነዉ። የቀድሞዉ የአሜሪካ የስለላ ድርጅት ባልደረባ ስኖዉደን፤ ይህን የገለፀዉ ባለፈዉ ሳምንት ሐሙስ የአረንጓዴ
ሙሉውን አንብብ-Read More

የራሱን ሚስጥር መጠበቅ ያቃተው የስለላ ድርጅት

Geez Bet | Tuesday, November 05, 2013
በአሜሪካ ስለላ ድፍን አውሮፓ ተናውጧል!
የመከላከያና የደህንነትን ነገረ ስራ ጉዳዬ ብለው የሚከታተሉ ባለሙያዎች፤ ሰላይና ተሰላይ በአንድ ጣራ ስር አድፍጠው የየፊናቸውን ጉዳይ የሚከውኑበት መስሪያ ቤቶች ቢኖሩ የስለላ ድርጅቶች ብቻ ናቸው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን እንዲህ ያለው ሁኔታ ሲያጋጥማቸው ሁሌም የሚጠቀሙበት አንድ አሪፍ አባባል አላቸው፡- “በሬ ካራጁ ይውላል” ይላሉ፡፡ 

የአሜሪካው የስለላ ድርጅት ሲአይኤ ይህ አባባል በረጅም የአገልግሎት ዘመኑ ለበርካታ ጊዜ ተጠቅሶበታል፡፡ በተደጋጋሚ ጊዜ ሌሎችን ለመሰለል የቀጠራቸው ሰላዮቹ፣ ራሱን መልሰው በመሰለል የመከዳትን መራራ ጽዋ ወዶ እስኪጠላ ድረስ ሲግቱት ኖረዋል፡፡
ኤንኤስኤ በሚለው አጭር ስያሜው ይበልጥ የሚታወቀው ብሔራዊ የደህንነት ድርጅት አሜሪካ ካሏት የተለያዩ የመረጃና የደህንነት ድርጅቶች አንዱ ነው፡፡ የዚህ ድርጅት የምሰረታ ታሪክ ልብወለድ ይመስላል፡፡
በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት የአሜሪካ የመገናኛና የኤሌክትሮኒክ ባለሙያዎች፤ የጀርመንንና የጃፓን ከፍተኛ ወታደራዊ ሚስጥሮችን ኮድ በመስበር በአሜሪካ ይመራ ለነበረው
ሙሉውን አንብብ-Read More

Nov 4, 2013

የ“ኢትዮ - ምህዳር” ጋዜጠኛ ከደረሰበት አደጋ ከሞት ተርፏል

Geez Bet | Monday, November 04, 2013
ለቀጣይ ህክምና 60ሺህ ብር ተጠይቋል
ጋዜጠኞች ገንዘብ ለማሰባሰብ መክረዋል
ከተመሰረት ጥቂት ወራትን ያስቆጠረው የ “ኢትዮ-ምህዳር” ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ ሚሊዮን ደግነው፣ ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ወርቁ እና አዘጋጁ ኤፍሬም በየነ ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ወደ ሀዋሳ የተጓዙት ለሽርሽር አልነበረም። በነጋታው ረቡዕ የፍ/ቤት ቀጠሮ ስለነበራቸው ነው፡፡
ከሁለት ሳምንት በፊት “ኢትዮ-ምህዳር”፤ ከሙስና ጋር በተያያዘ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዙሪያ በዘገበው ዜና ምክንያት፣ ዩኒቨርስቲው በጋዜጠኞች ላይ የ300ሺ ብር ክስ እንደመሰረተባቸው ይታወሳል። ጋዜጠኛ ኤፍሬም አብሯቸው የተጓዘው አንድም ዜናውን የሰራው እርሱ በመሆኑ፣ ተከራከሩ ቢባል ለፍ/ቤቱ በደንብ እንዲያስረዳ፣ ሁለትም የተከሳሽ ባልደረቦቹን የፍርድ ቤት ውሎ በአካል ተገኝቶ ለመዘገብ እንደነበር ዋና አዘጋጁ ጌታቸው ወርቁ ተናግሯል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ንግስት ሳባ አረብ ሳትሆን ኢትዮጵያዊት ንግስት ናት!

Geez Bet | Monday, November 04, 2013
በታላቁ መጽሃፍ “መጽሃፍ ቅዱስ” ላይ በመጽሃፈ ነገስት ቀዳማዊ ላይ በምዕራፍ 10 ከቁጥር 1 እስከ 13 ድረስ ንግስተ ሳባ ጠቢቡ ሰለሞንን ጎብኝታ ወደ ሃገሯ እንደተመለሰች ይናገራል፡፡ ዓረቦች ይህንን ታሪክ የግላቸው ለማድረግ መጠነ ሰፊ ጥረት አድርገዋል፤ ባይሳካላቸውም፡፡  
ንግስተ ሳባ የራሳቸው ንግስት በመሆን ጠቢቡን ጎብኝታ ለመመለሷ እንደ ማስረጃ የሚያነሱት በዓረቦች ውስጥ የሳባ ዓረቦች የሚባሉ ነገዶች ነበሩና የነሱም መጠሪያ ይህችው ሳባ ናት በማለት ነው፤ የርሷም መነሻ ዓረብ ነው በማለት፡፡ “ንግስተ ሳባ የኛ የሃገራችን ንግስት ሆና ጠቢቡ ሰለሞንን ለማየት ወደ ኢየሩሳሌም ከኢትዮጵያ ሳይሆን ከሃገራችን ተነስታ ሄደች፡፡” የሚልም በመጽሃፋቸው “በቁርዓን ሲራ 27” ላይ ሰፍሯል፡፡ የኛ ኢትዮጵያኖች ደግሞ “አይደለም ተሳስታችኋል… ንግስተ ሳባ ኢትዮጵያዊት ነች እንጂ እናንተ እንደምትሉት ዓረብ አይደለችም፡፡” በማለት ቀደምት አባቶቻችን ሞግተዋል፡፡ እኔም ከዚህ በኋላ በየደረጃው ኢትዮጵያዊት መሆኗን የሚያስረዱ ምክንያቶችን እያነሳሁ አልፋለሁ፡፡
ከቀደምት አባቶቻችን ከወረስናቸው የታሪክ መጽሃፍት እንደምንረዳው@ ንግስተ ሳባ ኢትዮጵያዊት ንግስት ብሎም የቀዳማዊ ምኒልክ እናት መሆኗን አረጋግጠናል፤ በዘመኗ ከመንግስቷ ኃያልነት የተነሳ የግዛቷ ስፋት የዓረብ ሃገራትን ያካትት ነበር፡፡ በመሆኑም እርሷ ጠቢቡን ለመጎብኘት ግዛቷ በሆኑ የዓረብ ሃገራት በኩል ለንጉሱ የሚሆን እጅ መንሻና አምኃ በግመሎቿ አስጭና እንደሄደች የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ፡፡ እነርሱ እንደሚሉት ዓረብ ሳትሆን ኢትዮጵያዊት ንግስት ነች፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

የጉዲፈቻ ልጃቸውን የገደሉ ተፈረደባቸው

Geez Bet | Monday, November 04, 2013
ኣንዲት የጉዲፈቻ ልጃቸውን ኣሰቃይተው ለሞት ያበቁ ባልና ሚስት አሜሪካውያን ከ28 እስከ37 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተፈረደባቸው።
የ13 ዓመትዋ ሐና ዊሊያምስ ህይወቷን ያጣችዉ በጎርጎሪዮሳዊዉ የዘመን ቀመር ግንቦት 12 ቀን 2011 ሲሆን ከትናንንት በስተያ ማክሰኞ ዕለት ያስቻለው የሲኣትል ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ ሚስት ወ/ሮ ካሪ ዊሊያምስ 37 ዓመት እና ባል ላሪ ዊሊያምስ ደግሞ 28 ዓመት እንዲታሰሩ ፈርዶባቸዋል።
ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ኣንድ ሌላ እትዮጵያዊ የጉዲፈቻ ልጅን ጨምሮ ሰባት አብራካቸዉ የተገኙ ልጆችም ኣሏቸው።
በ ዩኤስ አሜሪካ ከሴኣትል በስተ ሰሜን 60 ማይልስ ወይንም 100 ኪ ሜ ላይ በምትገኘው መለስተኛ ከተማ ሲድሮ ዊሊ ነዋሪ የሆኑት ካሪ ዊሊያምስ እና ባለቤትዋ ላሪ ዊሊያምስ የራሳቸው 7 የአብራክ ልጆች እያላቸው ከእነዚህ በተጨማሪ ያኔ ሐና ዓለሙ ትባል የነበረችውን ሙዋች ሐና ዊሊያምስን እና
ሙሉውን አንብብ-Read More

የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች

Geez Bet | Monday, November 04, 2013
የጋራ ማሕበር ለመመስረት የተስማማሙት ፖለከኞች እንደሚሉት የመጨረሻ አላማቸዉ ቢቻል ሁሉንም በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ተቃዋሚዎችን ይሕ ቢቀር ሰላሳ ሰወስት ፓርቲዎችን አስተባብሮ አንድ ጠንካራ ተቃዋሚ ጎራ ለመፍጠር ነዉ።ይሕ ምናልባት ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት በተቃዋሚዉ ጎራ የሚታየዉን መከፋፋል፥ መሰነጣጠቅና መጠላለፍ ለማስቀረት ይረዳ ይሆን?
    አስር የሚሆኑ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የጋራ ማሕበር ወይም ቅንጅት ለመመሥረት ተስማምተዋል። አደራጆቹ እንደሚሉት አሁን የጋራ ሕብረት የሚመሠርቱት ፓርቲዎች በሒደት በርካታ ፓርቲዎችን ከሚያስተናብረዉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ መድረክ ጋር የጋራ ትብብር ወይም ሕብረት የመመስረት እቅድ አላቸዉ።የጋራ ሕብረት ከሚመሠርቱት መካከል ደግሞ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ (አንድነት) ለመዋሐድ እየተወያዩ ነዉ።የጋራ ማሕበር ለመመሥረትም ሆነ ለመዋሐድ በሚደረጉት ዝግጅቶችና ዉይይቶች የማይሳትፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ደግሞ ሒደቱን ከሩቅ ማየቱን መርጠዋል።የዉይይት ዝግጅታችን የተቃዋሚ ፓርቲዎችን የትብብር እንቅስቃሴና የኢትዮጵያ ፖለቲካን ባጭሩ ይቃኛል።
ሙሉውን አንብብ-Read More