Time in Ethiopia:

May 29, 2014

Egypt’s presidential runner pledges to peacefully resolve dam row with Ethiopia

Geez Bet | Thursday, May 29, 2014
May 26, 2014 (ADDIS ABABA) – Egypt’s presidential front runner Abdel-Fattah al-Sisi said he would be keen to resolve the long running Nile water dispute with Ethiopia through dialogue if he is elected as the new president of the North African nation.
Presidential candidate and Egypt’s former army chief Abdel
 Fattah al-Sisi talks during a television interview
 broadcast on CBC and ONTV, in Cairo, May 6, 2014.
 (Photo Reuters-Al Youm Al Saabi Newspaper)
Al-Sisi said he was ready to visit Ethiopia for talks over the massive hydro plant project the East African country is building at the Blue Nile River.
Egypt fears the dam will diminish its water share and will eventually affect the country’s people, most of whom heavily rely upon the Nile’s water.
Just over a year ago Egyptian politicians were caught discussing whether to launch military attacks against Ethiopia to sabotage the construction of the multi-billion dollar power plant project.
The comments were made at a meeting hosted by the President Mohamed Morsi — who has since been deposed — when several politicians debated bombing the dam while unaware that television cameras were recording the discussion.
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 27, 2014

የአኖሌ ሃውልት ፖለቲከኞችንና ምሁራንን እያወዛገበ ነው

Geez Bet | Tuesday, May 27, 2014
ታሪኩ አፈ ታሪክ ነው፤ በደንብ ሊጠና ይገባዋል ተብሏል

በአፄ ምኒሊክ ዘመን ተፈጽሟል የሚባለውን ኢ-ሠብአዊ ድርጊት ለማሳየት በኦሮሚያ አርሲ ዞን አኖሌ በተባለ ስፍራ የተገነባው ሃውልት፤ የታሪክ ምሁራንን እና ፖለቲከኞችን እያወዛገበ ሲሆን፤ የታሪኩ እውነተኛነትና የሃውልቱ አስፈላጊነት አከራካሪ ሆኗል፡፡ 
ተቃራኒ አስተያየቶችን ለአዲስ አድማስ የሰጡ ፖለቲከኞች፤ ታሪኩ እውነተኛ ነው ወይስ አይደለም በሚለው ጥያቄ
አልተስማሙም፡፡ በአኖሌ ተፈጽሟል የተባለው ጡት እና እጅ የመቁረጥ ድርጊት በታሪክ ሰነዶች ያልተመዘገበና ያልተረጋገጠ አፈታሪክ ነው የሚሉ ፖለቲከኞች፤ ሃውልቱ ጥላቻና ቂም በቀልን የሚሰብክ ስለሆነ ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡ በአኖሌ ኢሰብአዊ ድርጊት መፈፀሙ እውነተኛ ታሪክ መሆኑን የሚያምኑ ፖለቲከኞች በበኩላቸው፤ ሃውልቱ  መገንባቱ ተገቢ የሚሆነው  ድርጊቱ እንዳይደገም መማሪያ ስለሚሆን ነው ብለዋል፡፡ 
ሙሉውን አንብብ-Read More

በፒያሳ ወርቅ ቤቶች ኮርኒስ ውስጥ ለ3 ቀን ያሸመቀው ወጣት ተያዘዘ

Geez Bet | Tuesday, May 27, 2014
በረሃብ ደካክሞ ለ5ቀን ራስ ደስታ ሆስፒታል ህክምና ተደርጎለታል:: 
ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ፒያሳ እምብርት ላይ በሚገኘው ዝነኛው ላሊበላ ወርቅ ቤት ውስጥ ለብዙዎች ትንግርት የሆነ ነገር ተከስቷል፡፡ ያውም በጠራራ ፀሃይ፡፡ ላሊበላ ወርቅ ቤት፤ በአካባቢው ከሚገኙ ሌሎች ወርቅ ቤቶች ለየት የሚያደርገው ለምሳ ከ7-9 ሰዓት መዘጋቱ ነው የሚሉት የወርቅ ቤቱ ባለቤት አቶ ኢዛና ካሣዬ፤ የዚያን ዕለት ግን ገበያ በመብዛቱ ለምሳ ሳይዘጋ እንደቀረ ይናገራሉ፡፡ 
የላሊበላ ወርቅ ቤት ትንግርት የተጀመረው ከጎኑ በሚገኘው ኢየሩሳሌም ወርቅ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ኮርኒስ ውስጥ የመንደፋደፍ ድምፅ እንደሰሙ የሚናገሩት የኢየሩሳሌም ወርቅ ቤት ሰራተኞች፤ ለጊዜው ቢደናገሩም “እርግብ ነው” በሚል ተስማምተው ወደ ስራቸው መግባታቸውን ይገልፃሉ፡፡ ሆኖም ድምፁ እየጨመረ በመምጣቱ ጥርጣሬ ይገባቸውና አንደኛው ሰራተኛ ክፍት በሆነው ኮርኒስ በኩል ባትሪ አብርቶ ተጠግቶ ይመለከታል፡፡ 
ኮርኒስ ውስጥ የሚንደፋደፈው እርግብ ሳይሆን ሰው መሆኑን ያረጋገጠው የወርቅ ቤቱ ሰራተኛ፤ “ሌባ… ሌባ” እያለ ሲጮህ ያልደነገጠ የለም፡፡ ኮርኒሱ ውስጥ ያሸመቀውን ወጣት ጨምሮ ሁሉም ድንብርብሩ ወጣ፡፡ ለማምለጥ የሞከረውም ወጣት ሲንደፋደፍ ከጎኑ ያለው የላሊበላ ወርቅ ቤት ኮርኒሱ ተቀዶ መሬት ሊፈጠፈጥ ሲል አንዱ የእንጨት ምሰሶ ደግፎት ይተርፋል፡፡  በዚህ ዱብዕዳ ወርቅ በመግዛት ላይ የነበሩ ደንበኞችና የወርቅ ቤቱ ሠራተኞች መደናገጣቸው አልቀረም፡፡ በዚህ ግርግር ወጣቱ ተመልሶ ወደ ኮርኒሱ  ውስጥ ይሸሻል፡፡ ይሄኔ ሁሉም ባለወርቅ ቤት በየራሱ ኮርኒስ ውስጥ ባትሪና ሻማ ይዞ በመግባት ወጣቱን ተጠርጣሪውን ማደን ጀመረ ይላል፤ የቅዱስ የብር ጌጣጌጥ መሸጫ ቤት ሠራተኛ ብርሃኑ አበበ፡፡ ተርታውን ያሉት የወርቅ መሸጫ መደብሮች የጥንት ቤቶች ስለሆኑ በኮርኒሳቸው ውስጥ ለውስጥ እንደሚገናኙ የነገሩን ሠራተኞቹ፤ ማታ ማታ ቤቱን ከመዝጋታቸው በፊት ወርቅና ብሮቹን ካዝና ውስጥ ከተው እንደሚቆልፉባቸው ገልፀዋል፡፡ 
በየግል ተጀምሮ የነበረው ወጣቱን የማደን ዘመቻ ከደቂቃዎች በኋላ በፖሊስ ሃይል ተጠናክሮ ቢቀጥልም ወጣቱ እምጥ ይግባ ስምጥ ሊታወቅ አልቻለም - ይላሉ አቶ ኢዛና፡፡ ከዚያም ጣራው አናት ላይ ወጥተው አሰሳውን ቀጠሉ፡፡ ወጣቱን ባያገኙትም ስለእሱ ድርጊቶች የሚጠቁሙ ፍንጮችን ለማግኘት እንደቻሉ የሚናገሩት አቶ ኢዛና፤ አንድ ቦታ ላይ ጣራው መቀደዱን ማየታቸውን፤ እዚያው አካባቢም ጣራው የተቀደደበት መቀስ መገኘቱን ገልፀዋል፡፡ወዲያው የተቀደደውን ቆርቆሮ በባለሙያ እንዳስደፈኑ ጠቁመው፤ አሰሳው ግን ያለውጤት መቋጨቱን ተናግረዋል፡፡ 
በነጋታው አርብ ጠዋት ደግሞ ቅዱስ የብር ጌጣጌጥ መሸጫ መደብር ውስጥ ሌላ ፍንጭ ተገኘ፡፡ በሩን ለመክፈት ሲሞክር የበሩ ቁልፍ (ጋን) እንዳስቸገረው የሚያስታውሰው ብርሃኑ፤ የቤቱን ባለቤት ጠርቶ አብረው ከፍተው መግባታቸውን ይገልፃል፡፡ ውስጡን ሲቃኙም አንዳንድ ነገሮች ተመሰቃቅለው ያገኛሉ፡፡ ወዲያው ፖሊስ ይጠሩና ሌላ የፍለጋ ዘመቻ ይጀመራል፡፡ ሆኖም ተፈላጊው አልተገኘም፡፡ 
ቅዳሜ ጠዋትም ብርሃኑ ከሱቁ ባለቤት ጋር ነበር በሩን የከፈትነው፡፡ የብር ጌጦቹን የሚደረድርበትን የመዝጊያ ብረት ሸርተት ሲያደርግ ነው ፈፅሞ ካልጠበቀው ነገር ጋር የተፋጠጠው፡፡ ሁለት ቀን መከራቸውን ያበላቸው ወጣት፤ ትልቅ የብር መስቀል በእጁ ይዞ መስተዋቱ ጋ ተለጥፎ ቆሟል፡፡ “ፊት ለፊት ቢያገኘኝ ግንባሬን ብሎኝ ወደ ውጭ ለመፈትለክ አስቦ እንደነበር ያስታውቅበታል” ያለው ብርሃኑ፤ በመስተዋት ውስጥና ውጭ ሆነን እንፋጠጣለን ብሎ የጠበቀ አይመስልም ብሏል፡፡ በሩን ከፍተው ሲገቡ ወደ ውስጥ ሊያመልጥ ቢሞክርም ወዴትም ሳይደርስ እንደያዙት የሚናገረው ብርሃኑ፤ ወዲያው  ተዝለፍልፎ መውደቁንም ገልጿል፡፡ ሰውነቱ ደካክሞና አቅም ክዶት እንደነበር በመግለፅም የምግብ እጥረት ሳያጋጥመው እንዳልቀረ ግምቱን ገልጿል፡፡ 
ወጣቱ ኪሱ ሲፈተሽ የብር ጌጦችና ጥቂት የወርቅ ቀለበቶች የተገኙበት ሲሆን ጀርባው ላይ ባዘለው ቦርሳ ውስጥ ደግሞ ውሃ፣ ቆሎ፣ መቀስ፣ ባትሪ እና የስለት መሳሪያዎች እንደተገኙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ተጠርጣሪው ወጣት ሰውነቱ በመጎዳቱና አቅም በማጣቱ፣ ራስ ደስታ ሆስፒታል ገብቶ ለአምስት ቀናት የህክምና እርዳታ የተደረገለት ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በአራዳ ክ/ከተማ ፒያሳ ፖሊስ ጣቢያ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ ፖሊስ ጠቁሟል፡፡ ፒያሳ የሚገኙ አብዛኞቹ ወርቅ ቤቶች በመደብራቸው ውስጥ እያንዳንዳቸው ከ2 ሚ.ብር ያላነሰ የወርቅና ብር ጌጣጌጦች እንዳላቸው ምንጮች ሲገልፁ፤ በዚህ ዓመት ብቻ በእነዚህ ወርቅ ቤቶች ከአራት ጊዜ በላይ የዝርፊያ ሙከራ እንደተፈፀመባቸው ፖሊስ ገልጿል፡፡ 
Source: Addis Admass

ሙሉውን አንብብ-Read More

May 23, 2014

ይድረስ ለአቶ ገብረ መድህን አርአያ ሊላክ ያልተፈለገ ግልጽ ደብዳቤ (ከበልጅግ ዓሊ)

Geez Bet | Friday, May 23, 2014
ሲሞላ ሲሞላ ጨዋታቸችን ሌላ፤
ሲጎድል ሲጎድል ሰው አንቀን ልንገድል።
የአማርኛ አባባል

እንደ መንደርደሪያ:- 
ጀሚላ  የትግራይ ልጅ የሆነች የኢሕአሠ(የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ሠራዊት) አባል ነበረች። በኢሕአፓ ታሪክ ውስጥ ከሚጠቀሱ ጀግና ሴቶች መካከል አንዷ ነች። የደርግን ፋሽሽታዊ መንግሥት በመቃወም በተደረገው ትግል ወቅት ወልቃይት ውስጥ ነበረች። በኢሕአፓ/ ኢሕአሠ በወቅቱ የነበረው ትግል ድርብ ነበር። ይኸውም  ከፋሽሽታዊ መንግሥትና ከዘረኛና ከአገር ገንጣዮች ጋር ኢሕአሠ ትግል ላይ ነበር። በዚህ ወቅት ነበር ጀሚላ በወያኔዎች እጅ የወደቀችው።  የትግራይ ልጅ በመሆኗ ቅጣቷ በወያኔ እጥፍ ድርብ ነበር። ግን የደረሰባት መከራ ከዓላማዋ ፈቀቅ አላደረጋትም። በቆራጥነት ዘረኝነትን እያወገዘች ወደ መገደያ ቦታ ትወስዳለች። እስከመጨረሻው በኢትዮጵያውነቷ እንደኮራች በጥይት ተደብድባ ትገድላለች። ዛሬ የጀሚላ ገዳዮች በሠሩት አሰቃቂ ግፍ ከሕሊናቸው ጋር ሲሟገቱ ጀሚላ በኢትዮጰያ ታሪክ ውስጥ በማይጠፋ ቀለም ተጽፋ አልፋለች። የጀሚላን የሕይወት ታሪክ የሚያውቁት ወደ ፊት በሰፊው እንደሚጽፉት አልጠራጠርም።
ተስፋዬ ደበሳይ የኢሕአፓ መሪና የትግራይ ሰው ነበር። ብዙዎቹ ጓዶቹ ይህንን ግለሰብ ያለውን ችሎታ ያደንቁታል። ተስፋዬ ደበሳይ አዲስ አበባ ውስጥ ከደርግ ጋር ሲፋለም ቆይቶ በመጨረሻም እጄን ለፋሽስቶች አልሰጥም ብሎ በኢትዮጵያውነቱ እንደኮራ ከፎቅ ዘሎ መስዋትነትን ከፍሏል። የእሱም ስም በማይጠፋ ቀለም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሰፍሯል።  ስለ ተስፋዬም የሕይወት ታሪክ ወደፊት በሰፊው ይጻፋል የሚል እምነት አለኝ።
ገብረእግዚያብሔር ጋይም ወያኔ ያስጨነቀ  የኢሕአፓ መሪ ነበር። ወያኔ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ በወያኔ ታጣቂዎች አዲስ አበባ ውስጥ ተገድሏል። ጋይም እስከለተ ሞቱ ድረስ ኢትዮጵያን ሳይከዳ፣ ዘረኝነትን እንዳወገዘ መስዋትነትን ከፍሏል።
ሙሉውን አንብብ-Read More

ብአዴን ማን ነው? (ገብረመድህን አርአያ – አውስትራሊያ)

Geez Bet | Friday, May 23, 2014
የአንድን ድርጅት ማንነቱን ከማቅረብ በፊት ቀደም ብሎ የተፈጸመውን ስህተት፣ ቀጥሎም ኢህአፓን ለማጥፋት በህወሓት እና በሻእቢያ የደረሰበትን ጥቃት አጠር ባለ መልኩ ማቅረብ አስፈላጊ ይሆናል።
የስትራተጂ ስህተት ለከባድ ወድቀት ይዳርጋል
ኢህአፓ ትግሉን የጀመረው ገና በ1960 መጀመሪያ ነበር። አብዮቱ እየተቀጣጠለ ሃገር አቀፍ ሆነ። ዘውዳዊ ስርዓት ወድቆ በማርክሲዝም ሌኒኒዝም ርእዮተ ዓለም የሚመራ ሶሻሊዝም የኢትዮጵያ ስርአት እንዲሆን ነበር። ይህ ግራ አክራሪ ስታሊኒዝም በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ ይማሩ በነበሩ የተሰባሰበ ቡድን፣ የወቅቱ አብዮተኞች ተገቢውን መልክ የያዘ አደረጃጀት ያልነበረው፣ አብዮተኛ የሚል ስም በማግኘታቸው ብቻ “ዲሞክራሲያ” ተብሎ የሚታወቀውን የኢህአፓ ልሳን በየሳምንቱ በመበተን አሁን ኢትዮጵያ የደረሰባትና እየደረሰባት ያለው ከባድ ችግር የከፈተው እነ ዋለልኝ መኮንን እና የኢህአፓ ግብረአበሮቹ የስታሊን ደቀ መዛሙርት ኢትዮጵያን አደጋ ወስጥ ጣሏት። በዚህ ወቅት ሰፊውን ትኩረት የሰጡት፤
  1. በኤርትራ ጥቅያቄ ላይ ኢህአፓ ያለው አቋም ኤርትራ ከዚህ ቅኝ አገዛዝ ነፃ በመሆን ተገንጥላ ነፃ መንግሥት ማቋቋም ሙሉ መብቷ መሆኑን ያምናል፤
  2. ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች ወህኒ ቤት እንደመሆኗ የኢህአፓ አቋም በዚሁ ጥያቄ ላይ ርቱእና ግልጽ ሲሆን፣ ብሄር ብሄረሰቦች የራሳቸውን እድል በራሳቸው በመወሰን እስከ መገንጠል መብታቸው ያልተገደበ ነው ይላል።
ይህ ትንታኔ ማንም ኢትዮጵያዊ በተጨማሪ ለማረጋገጥ ክፈለገ “ዲሞክራሲያ” ቅጽ 8 ቁጥር 1፣ የካቲት 23 ቀን 1973 የታተመውን ሙሉ ሃሳቡን በድጋሚ ጽፎታል፣ የቃላት ለውጥ በትንሹ ቢኖርበትም። ይህንን ጽሑፍ ለማግኘት EPRP በሚለው ድረገጽ በመግባት የዲሞክራሲያን እትም ከ1961 እስከ ዛሬ የሚለውን ፈልጋችሁ አንብቡ። ይህ ጽሑፍ የሚያሳዝነው ኢህአፓ አሲምባ እንደገባ ታጋዮቹ በፈጠሩት ጫና በሻእቢያ 1ኛ ጉባኤ 1969 መጨረሻ የአቋም ለውጥ በማድረግ
ሙሉውን አንብብ-Read More

ምኒልክን ብትወቅሱ ማንነታችሁን ትረሱ (ዶ/ር ኃይለማርያም ላሬቦ)

Geez Bet | Friday, May 23, 2014
በቅርቡ የአፄ ምኒልክን ስም የማጒደፍ ዘመቻ ያተኰረው ንጉሠ-ነገሥቱ በአሩሲ ውስጥ አኖሌ በተባለ ቦታ ፈጸሙ በተባለ ግፍ ላይ ነው። እንግዴህ “ሞኝና ውሃ እንደወሰዱት ይሄዳል” እንደሚባለው… ቅሌታም ብቻ ነው ልበ-ወለድን እንደእውነት፣ ምናብን እንደድርጊት አድርጎ የሚወስደው። ከዚያም አልፎ ደራሲው የታሪክ ባለሙያ መሆን ይቅርና የዐሥራ-ሁለተኛ ክፍል ትምህርት እንኳን ማጠናቀቅ ያልቻለ ግለስብ ነው። በዚህ በፈጠራ ጽሑፍ ተመሥርቶ ሐውልት የሚያሠራው ግለ-ሰብም ሆነ ባለሥልጣን በግድየሌሽነት የሕዝቡን ገንዘብ ማባከን ብቻ ሳይሆን፣ ሕዝቡን ራሱን ምን ያህል ወደኋላ የቀረ በማሰኘት በዓለምና በታሪክ ፊት እያስገመተ ነው። ርግጠኛ ነኝ የአኖሌ ሕዝብ የሚጠጣ ንጹህ ዉሃ፣ የሚመላለስበት ዘመናዊ መንገድና መጓጓዣ፣ በሽተኛውን የሚያስታምምበት የተደራጀ ሕክምና ቤት፣ ልጆቹን የሚያስተምርበት ማለፍያ ትምህርት-ቤትና፣ ትምህርቱንም ከጨረሰ ወዲያ የሚሰማራበት አስተማማኝ የሥራ ዘርፍ የለውም ይሆናል። የሐውልቱ ገንዘብ በተረት ላይ በተመሠረተ ድርጊት ከሚውል፣ በእነዚህ አገልግሎቶች ላይ ቢጠፋ፣ ሕዝቡን ምንኛ በጠቀመው፤ አሠሪውንስ ምንኛ ባስመሰገነው።
ሙሉውን አንብብ-Read More

በአባይ ጉዳይ ኃያላኑ በግብጽ ላይ ጫና እየፈጠሩ ነው

Geez Bet | Friday, May 23, 2014
ምዕራባውያን ሃያላን አገሮች ግብጽ በአባይ ዙሪያ የድርድር ጠረጴዛ ላይ እንድትቀመጥ ጫና እያደረጉ መሆኑ ተሰማ፡፡ ዜናውን የዘገበው አልአህራም ቃል በቃል ግብጽ ላይ ጫና ተፈጠረ ብሎ ባይጽፍም ከዜናው ለመረዳት እንደተቻለው ግብጽ ላይ ጫና እየተደረገባት ነው፡፡ ሃያላኑ ግብጽ ላይ እያሳደሩት ያለው ጫና መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ 
እንደ ጋዜጣው ዘገባ ያለፈው ቅዳሜ የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ከኢትዮጵያ ጋር በአባይ ጉዳይ ለመደራደር አገራቸው ፈቃደኛ መሆኗን ማሳወቃቸውን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ይህንን መግለጫ ከመስጠታቸው በፊት የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት የውሃ ሃብት ልዩ አስተባባሪ ከሆኑት አሮን ሳልዝበርግ እንዲሁም ከአውሮጳ ኅብረት ልዩ ልዑክ አልክሳንደር ሮንዶስ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ታውቋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ኢትዮጵያ የአባይ ወንዝ ባለቤት ናት? (ኪዳኔ ዓለማየሁ)

Geez Bet | Friday, May 23, 2014
መግቢያ፤ 
በጥንቱ ዘመን፤ የአባይ ወንዝ ዋናዋ ምንጭ ኢትዮጵያ መሆኗና ባለቤትነቱዋ ታውቆ፤ የግብጽ መሪዎች በየዓመቱ ለሚጎርፍላቸው ውሀ ይከፍሉ ነበር። ባሁኑ ጊዜ ግን፤ በተለይ ግብጽ የአባይን ወንዝ እንደ ግል ንብረቷ በመቁጠር ኢትዮጵያ በገዛ ወንዟ ለመጠቀም የምታከናውነውን ጥረት መቃወም ብቻ ሳይሆን ማስፈራራትም ይቃጣታል።
እንደሚታወቀው፤ ሰሞኑን በየድህረ-ገጹ በስፋት ከሚቀርቡት ሐተታዎች፤ ትችቶችና አስተያየቶች ውስጥ ሰፊ ስፍራ ይዞ የሚገኘው በኢትዮጵያ በመገንባት ስላለው ታላቅ የአባይ ግድብ ነው። ስለ ግድቡ የተንጸባረቁት የተለያዩ አስተያየቶች እንዳሉ ሆነው፤ የአባይ ወንዝ ባለቤትነት የማን እንደ ሆነ፤ ውሱን በሆነ መንገድ ተነካ እንጂ በጥልቀት በተከናወነ ምርመራና በዓለም-አቀፍ ሕግ ላይ በተመሠረተ አስተማማኝ ማስረጃ የተደገፈ ጽሑፍ አልቀረበም። የዚች ጦማር ዓላማም ኢትዮጵያ ከሱዳንና ከግብጽ ጋር በምታከናውናቸው ውሎች ያሁኑንና የመጪውን ትውልድ ሁሉ መብት በሚጠብቅ ሥልት መጠቀሟን እንድታረጋግጥ ተገቢውን ቅድመ-ዝግጅትና ጥንቃቄ እንድታደርግ ለማሳሰብ ነው። በዚህ አጋጣሚም፤ ተሞክሮው ለኢትዮጵያ የሚጠቅም ስለሚመስለኝ፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት፤ የለሶቶ (Lesotho) መንግሥት የሥራ ሚኒስቴር ቋሚ ተጠሪ በነበርኩበት ጊዜ ስለዛች ሐገር ወንዝ፤ በዓለም ባንክ ድጋፍ፤ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ጋር እኔ ራሴ በመራሁት የልዑካን ቡድን ስለ ተከናወነው ድርድርና ስለ ተገኘው ውጤትም ባጭሩ እገልጻለሁ።
ሙሉውን አንብብ-Read More

Ras Mekonnen Gudessa, the father of Emperor Haileselassie

Geez Bet | Friday, May 23, 2014
Mäkonnen Wäldä-Mika’él Guddisa, also Makonnen Wolde Mikael Gudessa (May 8, 1852 – March 21, 1906) or simply as Ras Makonnen, was a general and the governor of Harar province in Ethiopia, and the father of Tafari Mäkonnen (later known as Emperor Haile Selassie I). His father was Fitawrari[nb 2] Woldemikael Guddessa of a noble family of Oromo origin. Makonnen was a grandson of Negus[nb 3] Sahle Selassie of Shewa through his mother, Leult[nb 4] Tenagnework Sahle Selassie. As such, he was a first cousin of Emperor Menelik II.
en.wikipedia.org/wiki/Makonnen_Wolde_Mikael
A man of dignity Ras Mekonnen Gudessa of Shewa was the first dark skin official to ever enter the highest office and speak before the parliament members of Italy in Roma around the year 1899 just three years after the battle of Adwa.The barefooted royal figure has led a number of highly recognized Ethiopian delegates over several
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 21, 2014

ጅብ ከሚበላህ በልተኸው ተቀደስ – ከጸጋዬ ገብረ መድኅን አርአያ

Geez Bet | Wednesday, May 21, 2014
  ወያኔዎች አዲስ አበባን ከተቆጣጠሩ በኋላ የነበሩትን ዕለታት ክንውኖች በሥርዓት የመመዝገብ ልምድ ያለው ሰው የሚያሰፍራቸው ልዩ ልዩ ሁኔታዎች ይኖሩታል። ከመጀመሪያው ዕለት አንስቶ። የእኔን የመጀመሪያ ዕለት አጭር ማስታወሻ ልንገራችሁ። በማለዳ ተነስቼ ጋቢዬን አጣፍቼ ከበሬ ላይ ቆሜ ሥፍር ቁጥር የሌላቸው አህዮች ወደ መሐል ከተማው (አዲስ አበባ) ሲጓዙ አያለሁ። ያንኑ ያህል ባራባሶ ጫማ የተጫሙ፣ የአካል ዝለት የሚታይባቸውና ከእህል ጋር ከተለያዩ አያል ቀን የሆናቸው የሚመስሉ “ሰብአዊ ፍጥረቶች” አብረዋቸው ይሮጣሉ። ሲያሳዝኑ! ቆይ ቆይ…ከፓስተር ኢንስቲቱት በር ላይ አንድ ጥይት ተተኰሰ። ሌላ ጥይት- ሌላ ጥይት! ሰዎቹ ካለፉ በኋላ ወጣ ብለን ያየነው ሟች በሰፈሩ እንደ ሕሊና ሕመምተኛ የሚታወቅ ነበር። 

 እንግዶቹ አልመው የሚተኩሱ፣ አስበው የሚገድሉ አልመሰሉኝ አሉ። የሚያስቡበትና የሚያልሙበት ሕሊና የሌላቸው ፍጥረታት አድርጌ ላያቸው አልደፈርሁም። ባይሆን ሁሉም ጠላታችሁ ነውና አንዲት ጥይት ጮኸች ወይም አንድ ሰው ትንሽ ድምፅ አሰማ “በለው” በሚል መዘውር የተዘወሩ “መዘውራን” በመሆን በሳሩም በቅጠሉም ኤኬ47ቱን ማንጣጣት ያዙ። ያን ጊዜ በአእምሮዬ ጥግ በምትገኘው የማስታወሻ ሰሌዳዬ ላይ “ይኽ ቀን ገሐነም ባዶውን ያደረበት ዕለት ነው” ብዬ መዘገብሁ። እነዚህ ሰዎች እንደ መሪዎቻቸው በጥላቻ የተጠመቁ ከሆኑ መመለሻው ይቸግረናል። ከቶ ከየት ተነሥተን የት እንደርስ ይሆን? የማልረሳው ማስታወሻዬ ነው። 
ሙሉውን አንብብ-Read More

የግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ዕጩ ኢትዮጵያን በመጐብኘት በዓባይ ጉዳይ ለመደራደር ዝግጁ ነኝ አሉ

Geez Bet | Wednesday, May 21, 2014
-የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩም ግብፅ ለድርድር ፈቃደኛ ናት ብለዋል:: 
በግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ግንባር ቀደም ተወዳዳሪ የሆኑት አብዱልፈታህ አልሲሲ ኢትዮጵያን በመጐብኘት የሁለቱን አገሮች የዓባይ ውኃ ግጭት በውይይት ለመፍታት እንደሚጥሩ አስታወቁ፡፡
በተመሳሳይም የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ነቢል ፋህሚ የታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ግብፅ ከኢትዮጵያ ጋር ለመደራደር ፈቃደኛ መሆኗን መግለጻቸውን፣ የግብፅ ጋዜጣ አል አህራም ዘግቧል፡፡

ከ‘አል አህራም’ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የቀድሞው የጦር ኃይሉ መሪ አልሲሲ፣ ‹‹የግብፅና የኢትዮጵያን ቀውስ ለመፍታት ምርጡ መንገድ የሁለትዮሽ ድርድርና መግባባት ነው፤›› ማለታቸውም ተጠቅሷል፡፡ ከግጭትና ከጠላትነት ይልቅ ስምምነት የተሻለ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው የገለጹት አልሲሲ፣ ግብፅን የሚጠቅም ከሆነ ኢትዮጵያን ለመጐብኘት ዝግጁ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡ 
‹‹ይህ ወደ ግጭት ከመግባትና ከማንም ጋር ጠላት ከመሆን የተሻለ ነው፤›› ሲሉም አስታውቀዋል፡፡ 
የቀድሞ የግብፅ የጦር ኃይል አዛዥ የግብፅ የውኃ መብት ጉዳይ የሕይወትና የሞት ጉዳይ መሆኑን ግን አስረግጠው ገልጸዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 19, 2014

Egypt’s al-Sisi ready to visit Ethiopia for water talks

Geez Bet | Monday, May 19, 2014
Egypt’s presidential front runner Abdel-Fattah al-Sisi has said that he is ready to visit Ethiopia for talks on resolving their Nile water dispute.“Dialogue and understanding are the best way to resolve the crisis,” al-Sisi said in an interview with the state-run Al-Ahram daily on Saturday.“This is better than going into a dispute or an enmity with anyone,” he added.The former army chief, who led the army to unseat elected president Mohamed Morsi last July, said that he is ready to visit Ethiopia “if this serves Egypt’s interests”.“I will not hesitate in making any effort for my country and its water rights, which is a life-or-death issue,” he added.Relations between Cairo and Addis Ababa soured last year over Ethiopia’s plans to build a $6.4-billion hydroelectric dam on the Blue Nile, which represents Egypt’s primary water source.The project has raised alarm bells in Egypt, which fears a reduction of its historical share of Nile water.Water distribution among Nile basin states has long been regulated by a colonial-era treaty giving Egypt and Sudan the lion’s share of river water. Ethiopia, for its part, says it has never recognized the treaty.Source: .worldbulletin.net

ሙሉውን አንብብ-Read More

ኢትዮጵያና ግብፅ ያቋረጡትን ድርድር እንዲጀምሩ የአሜሪካ መንግሥት ጥሪ አቀረበ

Geez Bet | Monday, May 19, 2014
ኢትዮጵያ ለጀመረችው የታላቁ ህዳሴ ግብድ ግንባታ የአሜሪካ መንግሥት ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጠውና ግድቡን በተመለከተ የኢትዮጵያና የግብፅ መንግሥታት ያቋረጡትን ውይይት እንዲጀምሩ ጥሪ አቀረበ፡፡ 
የአሜሪካ ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ ባለፈው ረቡዕ የአሜሪካ መንግሥት ከሰሐራ በታች ላሉ የአፍሪካ አገሮች የሚሰጠውን ትኩረት አስመልክቶ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ አገሮች ከተወጣጡ ጋዜጠኞች ጋር ከአሜሪካ ሆነው በቀጥታ ቪዲዮ ኮንፈረንስ ተነጋገረው ነበር፡፡ ‹‹የአሜሪካ መንግሥት ከታላቁ የህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ ጋር በተገናኘ ከኢትዮጵያና ከግብፅ መንግሥታት ጋር ትልቅ ውይይት በማካሄድ፣ ሁለቱ አገሮች ልዩነታቸውን አቻችለው በጋራ እንዲሠሩ ጥሪ አቅርቧል፤›› ሲሉ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
 የአሜሪካ መንግሥት ኢትዮጵያ በመገንባት ላይ ባለችው የታላቁ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ ላይ ያለውን አቋም አስመልክቶ በተጨማሪ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ በመጀመሪያ በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል የሚስተዋለው የቃላት ጦርነት የአሜሪካ መንግሥትን እንደሚያሳስበው ገልጸዋል፡፡
ግድቡን በተመለከተ የአሜሪካ መንግሥት አቋም ሁለቱ መንግሥታት ወደ ንግግር መምጣት እንዳለባቸውና ተገናኝተው ሊወያዩ ይገባል፣ ያሉት ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሯ፣ ልዩነታቸውን ሊያስታርቁ ይገባል ሲሉ በአፅንኦት አስረድተዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ለፓትርያርኩ እንደራሴ እንደሚመደብ የሚገልጽ የሕግ ረቂቅ ለውይይት ቀረበ

Geez Bet | Monday, May 19, 2014


  • • ‹‹የፓትርያርኩን ሥልጣን ይገድባል›› በሚል ተተችቷል
  • ‹‹አመራራቸውን በብቃት እንዲያከናውኑ የሚያግዝ ነው›› /የሕግ ረቂቁ/
  • ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሚያስተላልፉት በብሔራዊ ቋንቋ ብቻ ይኾናል:: 

  • ከቤተ ክርስቲያኒቱ ዕድገትና ነባራዊ ኹኔታዎች ጋራ በማገናዘብ ያሻሽላል የተባለው የሕግ ረቂቁ ለውይይት የቀረበው፣ ባለፈው ረቡዕ ጀምሮ በመካሔድ ላይ በሚገኘው የቅዱስ ሲኖዶሱ ኹለተኛ ዓመታዊ መደበኛ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጎች ኹሉ የበላይ ነው የተባለው የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቁ÷ ርእሰ አበውና ለካህናቷና ለምእመናንዋ ኹሉ መንፈሳዊ አባት ለኾኑት ለፓትርያርኩ እንደራሴ እንደሚሾም በአንቀጽ 24 ላይ ማስፈሩ ተመልክቷል፡፡ እንደራሴው ‹‹ቅዱስ ፓትርያርኩ ከቤተ ክርስቲያን የተጣለበትን ሓላፊነትና መንፈሳዊ አመራር በሚጠበቀው ብቃትና ደረጃ ለማከናወን እንዲችል የሚያግዝ›› መኾኑ በሕግ ማሻሻያ ረቂቁ ተገልጧል፡ ፡

  •        የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ ፓትርያርኩን የሚያግዝ እንደራሴ እንደሚመደብ በሚገልጽና የፓትርያርኩን ሓላፊነትና ተጠያቂነት በጉልሕ የሚያሳዩ አንቀጾችን ባካተተ የሕግ ረቂቅ ላይ እየተወያየ እንደኾነ ተገለጸ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ በ1991 ዓ.ም. ያወጣችውን ሕግ ከሌሎች ሕጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር በማጣጣም፣
  • እንደራሴው የሚመደበው የቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት ብቻ በሚሳተፉበት ምርጫ ሲኾን፣ ለምርጫው ሦስት ዕጩዎች በፓትርያርኩና በቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት ጥቆማ እንደሚለዩ ተጠቅሷል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖት፣ ቀኖናና ትውፊት የማስጠበቅ እንዲሁም ያለአድልዎ የማስተዳደር ሓላፊነት ላለበት ለፓትርያርኩ በእንደራሴነት የሚመረጠው ሊቀ ጳጳስ ማሟላት የሚገባው መመዘኛ በሕጉ መመልከቱ የተጠቆመ ሲኾን መመዘኛው ለእንደራሴው ከ50 - 60 ዓመት የዕድሜ ገደብ ሲያስቀመጥ፣ የአስተዳደር ችሎታና የመንፈሳዊ አመራር ልምድን፣ መንፈሳዊና ዘመናዊ ዕውቀት አጣምሮ መያዝን እንደሚጠይቅም ታውቋል፡፡ ‹‹ግለሰባዊ የሥልጣን ፈላጊነት ስሜት የሚገንበት፣ የፓትርያርኩን ሥልጣን የሚጋፋና መካሠስን የሚያበረታታ ነው›› በሚል አንቀጹን የተቃወሙ የቤተ ክህነት ሓላፊዎች፣ ምደባው አስፈላጊ ኾኖ ከተገኘም እንደራሴው በፓትርያርኩ ጥቆማ ብቻ መመረጥ እንዳለበት የቃሉ ትርጉም እንደሚያስገደድ በመጥቀስ ይከራከራሉ፡፡
    የአህጉረ ስብከት የሥራ ሓላፊዎች በአንጻሩ፣ የእንደራሴው ምደባ፣ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ብልሹ አሠራር እንዲታረም የአደረጃጀትና የአሠራርለውጥ ጥናት በማድረግ ላይ ለምትገኘው ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አመራር መጠናከር የራሱ አስተዋፅኦ አለው በሚል እንደሚደግፉት ተናግረዋል፡፡ እንደራሴው ፓትርያርኩን ከማገዝ ውጭ ‹‹ለቅዱስ ፓትርያርኩ ከተሰጡት ተግባራት ውስጥ የሚጋራው የተለየ ሓላፊነት አይኖረውም፤›› በሚል በረቂቁ የሰፈረውን አንቀጽ በመጥቀስ ምደባው ፓትርያርኩን የመጋፋት ሚና እንደሌለውም ገልጸዋል፡፡ ተጠያቂነትን በተመለከተም ፓትርያርኩን ብቻ ሳይኾን ኹሉንም ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት ለቅዱስ ሲኖዶስ ተጠሪ ከማድረግ፣ በአስተዳደር በደልና በአመራር ጉድለት የካህናቱንና የምእመናኑን አመኔታና ተቀባይነት ማጣትን ጨምሮ ከሀብትና ንብረት ባለቤትነት ጋራ የተያያዙ ዝርዝር የተጠያቂነት አንቀጾች በረቂቁ በመካተታቸው በፓትርያርኩ አልያም በወቅታዊ እይታ ላይ ብቻ የታጠረ ረቂቅ እንዳልኾነ ያስረዳሉ፡፡
    ጉዳዩ በዋናነት የቤተ ክርስቲያኒቱን መንፈሳዊ አመራር ከማጠናከር አንጻር ሊታይ ይገባል የሚሉ አስተያየት ሰጭዎች፣ ምልዓተ ጉባኤው የሕግ ማሻሻያ ረቂቁን በጥልቀት በማዳበር የቅዱስ ሲኖዶሱ ሉዓላዊ ሥልጣን በማንም የማይገሠስበት መሣርያ አድርጎ እንደሚያጸድቀው እንጠብቃለን ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል፣ ፓትርያርኩ በቤተ ክርስቲያኒቱ ታላላቅ በዓላት ላይ እንዳስፈላጊነቱ እየተገኘ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሚሰጠው እንዲሁም በብዙኃን መገናኛ መንፈሳዊ መልእክት የሚያስተላልፈው በአገሪቱ ብሔራዊ ቋንቋ ብቻ እንደሚኾን በሕግ ማሻሻያ ረቂቁ ላይ መስፈሩ ተጠቅሷል፡፡
  • Source: Addis Admass

ሙሉውን አንብብ-Read More

May 16, 2014

የሀያኛውን ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ፖለቲካ የቀየሩ አነስተኛ ሰነዶች

Geez Bet | Friday, May 16, 2014
(አፈንዲ ሙተቂ):-
ይህንን አነስተኛ መጣጥፍ ከዚህ በፊት (በታህሳስ ወር 2006) ለጥፌው ነበር፡፡ ነገር ግን በርካታ ወዳጆቼ ከፌስቡክ ግድግዳህ ላይ ልናገኘው አልቻልንም” ስላሉኝ እንደገና መድገሙ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ለፍለጋ ቀለል የሚለው ብሎግ ስለሆነ በኔ ብሎግ ላይም እለጥፈዋለሁ፡፡
እነዚህ ሰነዶች በ20ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ አሳርፈዋል በማለት በዝርዝሩ ውስጥ የያዝኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ዝርዝሩ በሌሎች ምሁራንም ሆነ የጥናት ተቋማት እውቅና አልተሰጠውም፡፡ ማንም ሰው የክፍለ ዘመኑን የኢትዮጵያ የፖለቲካ አካሄድ ገምግሞ ከፍተኛ ተጽእኖ አሳድረዋል ያላቸውን ሰነዶች ሊጠቁም ይችላል፡፡ እኔም ይህንኑ ነው ያደረግኩት፡፡

ሰነዶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. አዕምሮ ጋዜጣ- 1904
2. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ህገ-መንግሥት- 1923
3. የኤርትራ ፌዴሬሽን ህገ-መንግሥት 1944
4. የተሻሻለው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ህገ-መንግሥት- 1948
5. የጀብሃ ቻርተር- 1954
6. የሜጫና ቱለማ ማህበር መተዳደሪያ ደንብ-1955
7. የብሄር ጥያቄ በኢትዮጵያ (በዋለልኝ መኮንን የተጻፈ ጽሑፍ)-1961
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 15, 2014

የወያኔ ጥላቻ ፍሬ

Geez Bet | Thursday, May 15, 2014
መስፍን ወልደ ማርያም:- 
ወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ ሲሰይመው፣ በአዲስ አበባ የተሠራውን መንደር መቀሌ ብሎ ሲሰይመው እየመሰከረ ነው፤ ‹‹የለሁበትም!›› እያለ ነው።
የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ
የትግራይ ሕዝብ መደህየቱ አልበቃ ብሎት ሲለምንም እየተሳቀቀ ነው፤ የሚለምነው ትግሬ ለብዙ ሰዎች ትግሬና ወያኔ አንድ መስሎ እንደሚታየው ያውቃል፤ አብዛኛው ሰው በወያኔ ላይ ያለውን ስሜት ያውቃል፤ ስለዚህም ሲለምን ሰዎች በወያኔ ላይ ያላቸውን ስሜት ስለሚያራግፉበት እየተሸማቀቀ ነው፤ አንድ የትግራይ ቄስ ከአርሲ ነኝ አሉኝና ለምን እውነቱን አይናገሩም ስላቸው እውነቱን ስናገር የማገኘው ስድብ ብቻ ነው አሉኝ፤ እኒህ ሰው ምን በወጣቸው የወያኔን ኃጢአት ተሸካሚ ይሆናሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በትግሬነቱ የተጠቀመ አለ፤ እኔ የማውቀው የደርግ ወታደር የነበረ ትግሬ ቆስሎ ከውትድርና ወጣና በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የጥበቃ ሥራ ላይ ነበር፤ በጣም ይቸግረው ነበር፤ ሚስቱ ሕመምተኛ ነበረች፤ የቤት ኪራይ መክፈል ይቸገር ነበር፤ ዛሬ ግን የሚለብሰው ልብስ
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 14, 2014

U.N. expecting to feed 6.5 million Ethiopians this year

Geez Bet | Wednesday, May 14, 2014
(Reuters) - The World Food Programme will help to feed nearly 6.5 million Ethiopians this year, the U.N. agency said on Tuesday, with the country hit by locusts, neighboring war and sparse rainfall. 
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 10, 2014

9 ጋዜጠኞችና ፀሐፊዎች ምን ሰርተው እንደታሰሩ እስካሁን አልተገለፀም

Geez Bet | Saturday, May 10, 2014
እስረኞች፤ ድብደባና ግርፋት ደርሶብናል አሉ::
         ከአለማቀፍ የመብት ተሟጋች ተቋም ጋር በገንዘብና በሃሳብ ተደራጅተው በኢንተርኔት አገሪቱን ለማሸበር አሲረዋል በሚል የታሰሩት 9 ጋዜጠኞችና የ“ዞን 9” ፀሐፊዎች ላይ ምርመራ እንዳልጨረሰ በመግለጽ ተጨማሪ ጊዜ እንዲፈቀድለት ፖሊስ የጠየቀ ሲሆን፤ ፍ/ቤት የ10 ቀን ቀጠሮ ሰጠ፡፡ ከሁለት ሳምንት በፊት ተጠርጣሪዎች ሀገሪቱን ለማሸበር በኢንተርኔት ማህበራዊ ሚዲያዎች አሲረዋል ያለው ፖሊስ፤ ሰሞኑን ተጠርጣሪዎቹ ፍ/ቤት ሲቀርቡ፣ የተያዙት በማህበራዊ ድረገፆች ላይ በፃፉት ሳይሆን ከውጭ አሸባሪ ኃይሎች ጋር በመደራጀት፣ አገሪቱን ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ለማሸበር እና የሽብር ሴራውንም ለመምራት ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸው ነው ማለቱን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ አመሀ መኮንን ተናግረዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ መንግስትን ከምርጫው በፊት ለመጣል፣ ከ5 ጊዜ በላይ እንደ ኬንያና ስውዲን ባሉ አገራት ስልጠና መውሰዳቸውን ፖሊስ ለፍ/ቤቱ ማስረዳቱንም ጠበቃው አክለው ገልፀዋል፡፡ በሶስት መዝገብ ተከፋፍለው በአራዳ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ጉዳያቸው የሚታየው ጋዜጠኞችና ፀሃፊዎች፤ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ለባለፈው ረቡዕ እና ሀሙስ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ መቀጠሩ
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 9, 2014

Breaking News: Abebe Gellaw interrupted Obama and Obama agrees with Ethiopia’s call for freedom

Geez Bet | Friday, May 09, 2014
San Jose, California–U.S. President Barack Obama has agreed with journalist Abebe Gellaw’s demand to support freedom in Ethiopia and help free bloggers, journalists and political prisoners jailed by the tyrannical regime.

While Obama was wrapping up his speech last night at a glitzy Democratic National Committee reception in San Jose’s Fairmont Hotel, journalist and activist Abebe Gellaw interrupted the president and called support for freedom in Ethiopia. The event jointly hosted by Yahoo CEO Marissa Mayer and and Y Combinator CEO Sam Altman was mainly attended by Silicon Valley business and political leaders.
Abebe began his message with a positive note. “Mr. Obama, we Ethiopians love you. We demand freedom for Ethiopia,” he said.
ሙሉውን አንብብ-Read More

Swiss court to try Ethiopian hijacker

Geez Bet | Friday, May 09, 2014
The co-pilot who hijacked an Ethiopian Airlines commercial passenger plane and demanded asylum in Geneva will not be extradited by his home country and will instead be tried in Switzerland on criminal charges.
The Swiss government refused to extradite him to Ethiopia, as confirmed by the Federal Office of Justice. Switzerland informed the Ethiopian government that the case against the hijacker had already been opened in Switzerland based on the same facts that were used to demand his extradition.

On the morning of February 17, Ethiopian Airlines flight 702 from Addis Ababa to Rome, carrying 200 passengers and crew, should have landed in Rome but instead continued on to Geneva after the co-pilot locked the pilot out of the cockpit and hijacked the plane, demanding asylum in Switzerland.
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 7, 2014

Egyptian troops fighting alongside the government caught in the battle of Ayod

Geez Bet | Wednesday, May 07, 2014
JONGLEI - A dozen of Egyptian soldiers fighting alongside the government of South Sudan were caught yesterday in a fierce battle with the rebels' white army in Ayod, Jonglei State. Government forces last week managed to capture Ayod after outmuscling hundreds of white
army stationed in that strategic town of Jonglei. The government after overrunning the white army burned down the commissioner's office building, market complex and all the huts within the town.
ሙሉውን አንብብ-Read More

3 Egyptians caught in Gambella, accused of spying

Geez Bet | Wednesday, May 07, 2014
GAMBELLA - The regional state government  of Gambella caught today 3 Egyptian nationals who penetrated to the the region via the war torn South Sudan in what the regional government of Ethiopia believed to be a spying mission to find information about the country's  Renaissance Dam. The the three men named as Yusuf Haj, Ismail Azizi and Hassan Garai were caught in separate locations of the region. 

Yusuf went to Abobo on a fake tourist pass to see the Abobo dam of the Abobo county (Woreda). The locals in Abobo worried about the suspicious activities he was making near the dam and that prompted his arrest by the local police. He was then transferred to the regional  administration in Gambella for further investigation and detentions.
ሙሉውን አንብብ-Read More

May 4, 2014

‹‹ኦሮሞነት አደጋ ውስጥ ገባ የሚለው ሚዛን የማያነሳ መፈክር ነው››

Geez Bet | Sunday, May 04, 2014

አቶ ኩማ ደመቅሳ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲ አማካሪ :: 
የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላንን በመቃወም በተለያዩ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲዎች የተነሳው ተቃውሞ ለኦሮሞነት ያላዘነ ባዶ መፈክር ነው ሲሉ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲ ጥናት አማካሪና የኦሕዴድ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ኩማ ደመቅሳ ገለጹ፡፡ 
አቶ ኩማ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ባስተላለፈው ፕሮግራም ላይ እንደተናገሩት፣ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተፈጠረው ተቃውሞና ውጥረት ሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች እንዳሉት፣ እነሱም ኦሮሚያን ቆርጦ ለማስቀረት የታለመ ማስተር ፕላን ነው የሚልና ፕላኑ ለምን በሚስጥር ተሠራ የሚል ሥጋት የፈጠሩት ናቸው ብለዋል፡፡ 
የተዘጋጀው ማስተር ፕላን ምንም ዓይነት የድንበር እንዲሁም የአስተዳደር ጥያቄ አለመያዙን የተናገሩት አቶ ኩማ፣ ሌላ የፖለቲካ ተልዕኮ ያላቸው ግን ጉዳዩን ከኦሮሞነት ጋር በማያያዝ የኦሮሞ ሕዝብን እያደናገሩ ነው ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ ‹‹ኦሮሞነት አደጋ ውስጥ ገባ የሚለው ባዶ መፈክርና ሚዛን የማያነሳ ክርክር ነው፤›› ያሉት አቶ ኩማ፣ ይህንን በማለት ለማደናገር የሚፈልጉ አጀንዳ ያላቸው ክፍሎችን ማብራሪያ በመስጠት መመለስ አይቻልም ብለዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More