Time in Ethiopia:

Apr 30, 2014

የታሰሩት ጋዜጠኞችና ጦማርያን ጉዳይ እያነጋገረ ነው

Geez Bet | Wednesday, April 30, 2014
-ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በነፃ እንዲለቀቁ እየጠየቁ ነው::
-መንግሥት አደገኛ ወንጀል ፈጽመዋል እያለ ነው::
የመብት ተሟጋቾች ነን ከሚሉ የውጭ ድርጅቶች ጋር በገንዘብና በሐሳብ በመስማማት፣ ሕዝብን ለአመፅ ለማነሳሳትና ለማተራመስ በኢንተርኔትና በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ ቀስቃሽ መጣጥፎችን ለማሰራጨት ሲዘጋጁ ተደርሶባቸዋል በሚል፣ በወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ ጋዜጠኞችና ጦማርያን (Bloggers) ጉዳይ እያነጋገረ ነው፡፡


ሚያዝያ 25 እና 26 ቀን 2006 ዓ.ም. በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ በ48 ሰዓታት ውስጥ በዕለተ እሑድ ሚያዝያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት በቀረቡበት ወቅት፣ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል (ማዕከላዊ) መርማሪ ፖሊስ፣  ተጠርጣሪዎቹ ከውጭ ድርጅቶች ጋር በገንዘብና በሐሳብ ተስማምተው ሕዝቡን ለአመፅ ለማነሳሳት ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል ከሚል የወንጀል የጥርጣሬ ውጪ ያለው ነገር ስለሌለ፣ ‹‹ወንጀሉ ምድነው?›› የሚል ጥያቄ ከማንሳት ጀምሮ የተለያዩ መላ ምቶችን በማንሳት የተለያዩ አካላት እየተነጋገሩበት ነው፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 28, 2014

ብቸኛው ሰው (ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም)

Geez Bet | Monday, April 28, 2014
 ጸሓፊ፡-አፈንዲ ሙተቂ:-
ፕሮፌሰር መስፍንን በአካል ያየሁት ሁለት ጊዜ ያህል ብቻ ነው፡፡ በነዚህም ጊዜያት ከመጨባበጥ በቀር ሌላ ነገር ማውጋት አልቻልንም፡፡ ብንጨዋወት እንኳ በፖለቲካ አመለካከታችን የምንግባባ አይመስለኝም፡፡ ለምሳሌ እሳቸው “ኢትዮጵያ ውስጥ ነገዶችና ጎሳዎች እንጂ ብሄሮችና ብሄረሰቦች የሉም፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አንድ ብሄር ብቻ
ነው” ነው የሚሉት፡፡ እኔ ግን “በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሉ፤ ነገድና ጎሳ የብሄር ቅርንጫፎች እንጂ ራሳቸውን የቻሉ ህዝቦች አይደሉም” ነው የምለው፡፡ በሌላ በኩል ፕሮፌሰር መስፍን “የብሄረሰቦችን መብት ለማስከበር በብሄር መደራጀቱ ለሀገር አንድነት አደጋ አለው” የሚል እምነት አላቸው፡፡ እኔ ግን “ለመጥፎ ዓላማ እስካልሆነ ድረስ በብሄር መደራጀቱ መጥፎ አይደለም” የሚል እምነት አለኝ፡፡ ሌላም ብዙ ልዩነት ማስቆጠር ይቻላል፡፡
ይሁንና በፖለቲካ እንዲህ የተለየኋቸውን ምሁር ለአንድም ቀን እንደ ጠላት አይቼአቸው አላውቅም፡፡ በተቃራኒው ህሊናን በሚያምራምሩ ብዙ ባህሪያቶቻቸው በጣም ያስቀኑኛል፡፡ “እኛስ መቼ ነው እንደርሳቸው ሆነን ለሀገራችንና ለህዝባችን ክብር የምንቆረቆረው” እላለሁ፡፡ ከዚህ ፈቅ የሚሉት አንዳንድ አድራጎታቸው ግን በነቢያትና በቅዱሳን ካልሆነ በቀር ከኛ ዘመን ሰው የሚጠበቁ አይደሉም፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

የክርስቲያንና የሙስሊም ፍቅር በገለምሶ

Geez Bet | Monday, April 28, 2014
ጸሓፊ፡-አፈንዲ ሙተቂ:-
 ከጥቂት ሳምንታት በፊት ስለገለምሶው መምሬ ሙላቱ የምትተርክ አንዲት ጽሑፍ ለጥፌ ነበር፡፡ አሁን ሳስበው ግን ያቺ ጽሁፍ መሀል መንገድ ላይ ተቆርጣ የቀረች ሆና እየታየችኝ ነው፡፡ ስለዚህ ለናንተም፤ ለወገንም፣ ለታሪክ ጸሓፊያንም እንዲጠቅም ይህችኛዋን ሐተታ እጨምርበት ዘንድ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

  በ1981 የስድስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ይመስለኛል፡፡ ከትምህርት ቤት መልስ የጨዋታ ጓዶቼን ፍለጋ “ኒብራ” ከተሰኘው የገለምሶ ከተማ ዋነኛ ጎዳና ወረድኩ፡፡ ጓዶቼን ብዙም ርቀት ሳልሄድ ከትልቁ የጋሽ መሐመድ በከር መደብር በረንዳ ላይ አገኘኋቸው፡፡ እዚያም የኳስ ጨዋታ ሰዓታችን እስኪደርስ ድረስ በትረባና በፉገራ መናቆር ጀመርንና አንዱ ሌላውን ለማብሸቅ ይሞካክር ገባ (በጊዜው ትረባ፣ ፉገራና ለከፋ ጊዜያችንን የሚገፋልን ትልቅ መዝናኛችን ነበር)፡፡ እኛ የነበርንበትን በረንዳ በስተግራ በኩል ተጎራብቶ ወደ ታላቁ የሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድና “ሐድራ” ወደሚባለው እስላማዊ ማዕከል (መስጊዱ የሐድራ አንድ ክፍል ነው) የሚያስወጣ መንገድ አለ፡፡ መንገዱ በወቅቱ በጎርፍ ክፉኛ ተጎድቶ ስለነበር ወደ አስር የሚደርሱ የቀን ሰራተኞች ድንጋይ እየቀጠቀጡ የተቦረቦረውን የመንገዱን የመሀለኛውን ክፍል ይሞሉትና በድንጋዩ ላይ አሸዋ እየመለሱ ይደመድሙት ነበር፡፡
ይህ የምላችሁ መንገድ በጎርፍ የተጠቃው በዚያን ጊዜ ብቻ አይደለም፡፡ ዘወትር ክረምቱን ጠብቆ ከካምቦ ተራራ በሚወርደው ሀይለኛ ጎርፍ እየተደረመሰ አሳሩን ያያል፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት በመንገዱ ዳርና ዳር የፍሳሽ መውረጃ ቢሰራለትም ጎርፉ በጣም ከባድ በመሆኑ የተሰራለትን መውረጃ በመተው ወደ መሀል መንገድ ዘው ብሎ እየገባ መንገዱን ማበላሻሸቱ የየዓመቱ ትዕይንት ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ መኪና ይቅርና ሰዎችና የጋማ ከብቶችም በዚያ ዳገታማ መንገድ ሲወጡና ሲወርዱ መከራቸውን ነው የሚያዩት፡፡
ክረምቱ ካለፈ በኋላ መንገዱ ይጠገናል፡፡ ጥገናው የሚከናወነው በአብዛኛው በነጋዴ ግለሰቦች እንጂ በማዘጋጃ ቤቱ አይደለም፡፡ ታዲያ ከላይ በጠቀስኩትና ወሩንና ቀኑን በዘነጋሁት የ1981 አንደኛው ዕለት መንገዱን የሚያስጠግነው ግለሰብ ከወትሮው የተለየ ሆነብኝና በደንብ አየሁት፡፡
ሰውየው ቄስ ነው፡፡ መንገዱ ደግሞ ወደ መስጊድ የሚያስወጣው ትልቁ መንገድ፡፡ ቄሱ ወደ መስጊድ የሚያስወጣውን ትልቁን መንገድ ያስጠግናል!! አጃዒብ! በልጅነት አዕምሮዬ ተገረምኩ፡፡ በጣም ተደመምኩ፡፡ እናም በአቅራቢያችን የነበሩትን ጋሽ መሐመድ በከርን ስለሰውየውና ስለመንገድ ጥገናው ጠየቅኳቸው፡፡
“ዛሬ መንገዱን የሚያስጠግነው ቄስ ነው እንዴ?”
“አይ ቄሱ ሳይሆን ቤተክርስቲያን ነው”
“የቱ ቤተክርስቲያን?”
“መድኃኒ ዓለም ቤተክርስቲያን ነዋ! በገለምሶ ስንት ቤተክርስቲያን ነው ያለው?”
“ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል? የመስጊድን መንገድ ነው እንዴ ቤተክርስቲያን የሚያስጠግነው?”
“እንዴት ሊሆን አይችልም? እነርሱስ ቢሆኑ የኛ ሰዎች አይደሉም እንዴ? እኛስ ቤተ ክርስቲያናቸው በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ቢጠቃ ዝም ብለን እናያለን እንዴ?”
ጋሽ መሐመድ የነገረኝ ነገር እውነት መሆኑን በደንብ ያረጋገጥኩት በአስር ሰዓት ገደማ ቄሱ ለሰራተኞቹ ክፍያ በፈጸሙበት ወቅት ነው፡፡ በነጋታውም እኒያ ቄስ ሰራተኞችን አሰማርተው መንገዱን ሲያስጠግኑ ነበር የዋሉት (እኚያ ቄስ የአካባቢያችን ተወላጅ አልነበሩም፤ ለዚህም ነው ስማቸውን ያልያዝኩት፡፡ ሆኖም ቀጠን ብሎ ዘለግ ያለው ሰውነታቸው፣ ጠይም መልካቸውና ሰልካካ አፍንጫቸው እስከ አሁን ድረስ ይታወሱኛል፤ ብዙ ጊዜም ሰማያዊ ቀለም ያለው ቆብ ነው በራሳቸው ላይ የሚያደርጉት)፡፡
ልብ ያለው ይበል! እንዲህ አይነት ታሪክ በገለምሶ ተፈጽሟል፡፡ የገለምሶ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን ወደ ሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድ የሚያስወጣውን መንገድ በራሷ ገንዘብ አስጠግናለች፡፡ በገለምሶ የክርስቲያንና ሙስሊሙ ፍቅር እስከዚህ ድረስ ነበር፡፡ ዛሬ በአካል እዚያ ባልኖርም ይህ የጥንት ፍቅራችን አሁንም ድረስ እንዳልቀዘቀዘ ቤተሰቦቼ ያወጉኛል፡፡
***** ***** *****
“የሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድስ ለክርስቲያኖችና ለቤተክርስቲያኒቷ ምን አድርጎ ያውቃል?” ብላችሁ መጠየቃችሁ አይቀርም መቼስ! እንዲያ ከሆነ የሚከተለውን ታሪክ ላጋራችሁ፡፡
የሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድ “ሐድራ” የሚባለው እስላማዊ ማዕከል አንዱ ክፍል ነው- ከላይ እንደጠቀስኩት፡፡ ይህ ሐድራ የሚባለው ማዕከል ከትልቁ መስጊድ ሌላ የቁርአን መማሪያ (ቁርአን ጌይ)፣ የዒልሚ መማሪያ (ቤይተል ዒልሚ)፣ የሴቶች መማሪያና መስገጃ፣ የዚክሪና አውራድ ማድረጊያ፣ የአዛውንቶችና የሽማግሌዎች መኖሪያና ሌሎች በርካታ ቤቶች አሉት፡፡ እንዲሁም “ቤይቱል ሐድራ” የሚባለውና የሁሉም እንግዶች ማረፊያ የሆነው ቤት (በስፋቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲውን ልደት አዳራሽ የሚያክል) በዚሁ ሐድራ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ እነዚህ ቤቶች ሁሉ ከዓመት እስከ ዓመት ተመሳሳይ አገልግሎት ነው የሚሰጡት፡፡ በመውሊድ ጊዜ ግን አገልግሎታቸው ይቋረጥና በበዓሉ ለመታደም የሚመጡትን እንግዶች ያስተናግዳሉ፡፡ በየቤቶቹ ውስጥ ሰለዋትና መንዙማ ይደረጋል፡፡
በገለምሶ የሚከበረው መውሊድ ሞቅ ደመቅ ያለ ነው፡፡ በበዓሉ ላይ የሚታደሙ እንግዶች ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍለሀገራት ይመጣሉ፡፡ ከዚህም አልፎ ከጎረቤት ሀገራት ጭምር (ሶማሊያ፣ ጅቡቲ እና የመን) በርካታ ሰዎች ይመጣሉ፡፡ እነዚህን እንግዶች ለማስተናገድ በትንሹ አስራ አምስት በሬዎችና ሶስት ግመሎች ይታረዳሉ፡፡ ግመሎችና በሬዎቹን የሚገዙት ግን የሐድራው ሰዎች አይደሉም፡፡ ድሮ በሼኽ ዑመር አሊዬ እጅ የተማሩ ሼኮችና ሌሎች የሼኽ ዑመር ወዳጆች ናቸው ከብቶቹን የሚያመጡት፡፡
ታዲያ የሐድራው ሀላፊዎችና የመስተንግዶ መሪዎች ወደነርሱ የሚመጡትን ከብቶች በሙሉ አያርዷቸውም፡፡ በቅድሚያ አንድ ወይም ሁለት በሬ ለሴቶች ይሰጥና የከተማው ሴቶች ከልዩ ልዩ ክፍለ ሀገራት የሚመጡ ወይዛዝርትን እንዲያስተናግዱበት ይደረጋል (በሐድራ ውስጥ ሴትና ወንድ መቀላቀል ክልክል ነው፤ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ምግባቸውን ለየራሳቸው ነው የሚያዘጋጁት፤ ደግሞም የሁለቱም ጾታ ሰዎች ከተፈቀደላቸው ክልል ውጪ መውጣት የለባቸውም)፡፡
በማስከተልም አንድ በሬ ለስጋ ደዌ በሽታ ተጠቂዎች ይሰጣል፡፡ እንዲህ የሚደረግበትን ምክንያት በትክክል ባላውቅም በዘመኑ በነበረው ልማድ የተነሳ የበሽታው ተጠቂዎች መሸማቀቅ ሳይደርስባቸው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተናግዱ ማድረጉ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ ይመስለኛል፡፡ በሬዎቹ ለሴቶችና ለስጋ ደዌ ህሙማኑ የሚላኩት ግን ለግብዣና ለፌሽታ ብቻ አይደለም፡፡ በመስተንግዶው የሚታደሙት ሰዎች ሰለዋት ስለሚያደርጉና የነቢዩን ገድል በመንዙማ ስለሚያወድሱ ነው፡፡ እንዲያ የማያደርግ ጀመዓ ለመውሊድ ከመጣው በሬ አንዳች ድርሻ የለውም፡፡
ነገር ግን ይህ መመሪያ የማይመለከተው አንድ ክፍል አለ፡፡ የገለምሶ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን! በዓሉን የማታከብር ሆኖም ከመውሊድ በሬዎች የራሷ ድርሻ የነበራት ብቸኛ አካል እርሷ ነበረች፡፡ ለዚያውም ለርሷ የሚደርሳት አንድ በሬ ብቻ አይምሰላችሁ! ሁለት በሬዎችን ነው በየዓመቱ የምታገኘው፡፡
የዚህ ምክንያት ለረጅም ጊዜ ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ዕድሜዬ ከፍ ካለ በኋላ ግን ምክንያቱን የሐድራው መሪ የሆኑትን ሼኽ ሙሐመድ ሲራጅን ጠይቄ ከአንደበታቸው ተረዳሁ (ሼኽ ሙሐመድ ሲራጅ የሐድራው መስራች የነበሩት የሼኽ ዑመር አሊዬ ልጅ ናቸው- አሁን ዕድሜአቸው ከዘጠናው ተሻግሮ ወደ መቶ ዓመት እየተጠጋ ነው)፡፡
ሼኽ ሙሐመድ ሲራጅ ሁለት በሬዎች በየዓመቱ ለቤተክርስቲያን የሚሰጥበትን ምክንያት እንዲህ በማለት ነበር ያስረዱኝ፡፡
“እነዚህ ክርስቲያኖች ወንድሞቻችን ናቸው፡፡ እንደኛው የአዳም ልጆች ናቸው፡፡ በሀይማኖት ብንለያይም የአንድ ሀገር ሰዎች ነን፡፡ ከዚያም አልፎ የአንድ ከተማ ነዋሪዎች ነን፡፡ በሬዎቹ ወደኛ የሚመጡት በዓላችንን በደስታ ለማክበር እንድንችል ነው፡፡ እኛ በሬዎቹን አርደን በዓላችንን በደስታ ስናከብር ክርስቲያን ወገኖቻችንን መዘንጋት የለብንም፡፡ እስልምናችን ጎረቤቶቻችንንም ማስደሰት እንዳለብን ያዘናል፡፡ ስለዚህም ነው በሬዎቹን ወደ ቤተክርስቲያን የምንልከው”፡፡
***** ***** *****
እንዲህ ዓይነቱን ውብ ባህል ምንድነው የምትሉት? “መቻቻል” ነው የሚባለው ወይስ ሌላ ስም አለው? እኔ ግን “መቻቻል” አልለውም፡፡ ይህ በተመን የማይመነዘር ፍቅር ነው እንጂ “መቻቻል” የሚለው ዘመን ወለድ ታፔላ የሚለጠፍለት አይሆንም፡፡ “መቻቻል” ሲባል አንዱ ወገን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ሌላውን የሚያስከፋ ድርጊት በሚፈጽምበት ጊዜ ሌላኛው ወገን በትዕግስት ችሎ ማለፍ ይገባዋል የሚል እድምታ ያለው ይመስለኛል፡፡ በኔ ከተማ ግን ፍቅር ሰባኪ የሆኑት ሼኮች እና ቄሶች ክፋት ሊፈጸም የሚችልባቸውን ሽንቁሮች ሁሉ ቀድመው የደፈኗቸው በመሆኑ “መቻቻል” የሚባለው አነጋገር እዚያ ዘንድ ተራ ጉዳይ ነው የሚሆነው፡፡ በዚያች እትብቴ በተቀበረባት መሬት ያየሁትና የሰማሁት “ፍቅር” ነው እንጂ “መቻቻል” አልነበረም፡፡
በኔዋ የገለምሶ ከተማ እንዲህ ዓይነት ፍቅር ነበረን፡፡ በሌላው ኢትዮጵያስ ቢሆን? ዲግሪው (መጠኑ) ይለያይ ይሆናል እንጂ ተመሳሳይ ታሪኮች ሞልተዋል፡፡ እንዲህ በህብረት የኖረውንና ፍቅርን የተቋደሰውን ህዝብ የፖለቲከኞች ወሬ ሆድና ጀርባ ሊያደርገው ከቶ አይቻለውም፡፡ ፖለቲከኞች ይህንን በሌሎች ሀገራት በስለት እንኳ ተፈልጎ የማይገኝ ውብ ባህላችንን በዓለም ዙሪያ ቢያስተዋውቁልን ነው የሚያምርባቸው፡፡
እኛ አንድ ነን፡፡ ወንድማማቾች ነን፡፡ ፍቅር ነን፡፡ ክብር ነን፡፡ ህብር ነን፡፡ ሰሞነኛ ወሬ አያለያየንም፡፡

አፈንዲ ሙተቂ
ነሐሴ 21/2005


ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 23, 2014

በምስራቅ ወለጋ ዜጎች እየተፈናቀሉ ነው

Geez Bet | Wednesday, April 23, 2014
በምስራቅ ወለጋ ስቡ ስሪ ወረዳ ‹‹ይህ አገር የእናንተ አይደለም፡፡ አገራችሁን ግቡ፡፡›› በሚል 200 ያህል አርሶ አደሮች እንደተፈናቀሉ አስታወቁ፡፡ በ1990ዓ.ም ጀምረው በአካባቢው የኖሩት እነዚህ ዜጎች ‹‹የመኖሪያ መታወቂያ ተሰጥቶን፣ ውጡ
ምሬታቸውን ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ ከዚህ ቀደም በ1992 በተመሳሳይ ቤትና ንብረታቸው ወድሞ ተፈናቅለው የነበረ ቢሆንም መንግስት እንደገና እንዳቋቋማቸው ይገልጻሉ፡፡ ‹‹በአንድ በኩል አገራችሁ አይደለም ውጡ!›› የሚሉት የአካባቢው ባለስልጣናት በሌላ በኩል ደግሞ ‹አካባቢውን ልንሰራበትና ልናሰራበት ነው ይሉናል፡፡ በ1992ም መንግስት እንደገና አቋቁሞናል፡፡ አሁንም ቦታው ከተፈለገ መንግስት ተገቢውን ካሳ ሊሰጠን ይገባል፡፡› ብለን ስንጠይቅ ደግሞ ‹እናንተን መንግስት አያውቃችሁም፡፡ በምስራቅ ወለጋ ዜጎች እየተፈናቀሉ ነው ይሉናል› በሚል እየደረሰባቸው ያለውን ህገ ወጥ ተግባር ይናገራሉ፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

አርሶ አደሮች መሬታቸውን ያለካሳ እየተነጠቁ ነው

Geez Bet | Wednesday, April 23, 2014
መራዊ፡- በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ያለ ፈቃዳችን መሬታቸውን አሳልፈን አንሰጥም ያሉ አርሶ አደሮች እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በመራዊ አካባቢ ሜጫ ወረዳ እናሸንፋለን ቀበሌ መንግስት
የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ እናካሂዳለን በሚል ከ400 በላይ የሚሆኑ አርሶ አደሮች ከመሬታቸው እንዲለቁ የተደረገውን እርምጃ አርሶ አደሮቹ በመቃወማቸው እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በአካባቢው ከአሁን ቀደም ተመሳሳይ እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን የአርሶ አደሮቹ መሬት በአበባ ኢንቨስትመንት ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ተሰጥቶባቸዋል፡፡ 
         ይህም በአሁኑ ወቅት መንግስት ውሃ ለመቆፈር በሚል አርሶ አደሮቹ ከመሬታቸው እንዲለቁ የሚወስደው እርምጃ በተመሳሳይ  ለአበባ እርሻ ሊሰጥባቸው እንደሆነ በማመናቸው ከመሬታቸው አንለቅም ብለዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 16, 2014

አርሶ አደሮች የመሬት ይዞታ ደብተራቸውን ተቀሙ

Geez Bet | Wednesday, April 16, 2014
•‹‹እቃችንን ሽጠን ፈቃዳችን እንመልሳለን›› ነጋዴዎች:: 
ደብረ ማርቆስ፡- በምስራቅ ጎጃም ዞን ከአምስት በላይ ወረዳዎች ውስጥ መንግስት የአርሶ አደሮችን የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር እየሰበሰበ መሆኑ ተሰማ፡፡ በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎዛምን፣ ባሶ ሊበን፣ አንደድና ሌሎችም ወረዳዎች የመሬት አስተዳደርና የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሰራተኞች መሬቱን እንደገና ለማጥናት እንዲሁም የግልና የመንግስት ይዞታን ለመለየት በሚል የይዞታ ማረጋገጫ ደብተሮችን እየሰበሰቡ መሆኑን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያስረዳል፡፡
ምንም እንኳ የይዞታ ደብተሩን ሰብሳቢዎቹ በይፋ ለጥናት እንዲሁም የመንግስትና የግል ይዞታን ለመለየት ነው ቢሉም ካድሬዎች ‹‹ኢህአዴግን ካልመረጣችሁ መሬታችሁን እንነጥቃችኋለን፡፡ መሬት የምንሰጠው እኛን ለመረጠ ብቻ ነው፡፡›› በሚል እያስፈራሯቸው እንደሆነ አርሶ አደሮቹ ባደረሱን መረጃ ገልጸዋል፡፡
አቶ ሳሙኤል የተባሉ የህግ ባለሙያ ከስፍራው እንደተናገሩት ደግሞ፣ ‹‹ደብተሩ ገበሬዎች መሬቱ የራሳቸው ስለመሆኑ ለማረጋገጥ፣ ለግንባታ ወይንም ለሌላ ነገር ቢሰጥ ካሳ ለማግኘት፣ በህገ-ወጥ መንገድ ቢያዝም ለመከራከሪያነት የሚያገለግል በመሆኑ የይዞታ ማረጋገጫውን የሚሰበስቡት በይፋ ከሚሰጡት ምክንያት በስተጀርባ መሬትን ለ2007 ምርጫ መያዢያነት ለመጠቀም ስላሰቡ ነው፡፡ ደብተር ከሌላቸው ግን መሬቱ የእነሱ አይደለም ማለት ነው፡፡ አርሶ አደሩ የይዞታ ደብተሩ ከእጁ ከሌለ የመሬት ባለቤትነቱ ተስፋውን ስለሚያጣ የግዱን ይመርጠናል ከሚል ፖለቲካዊ ምክንያት ነው›› ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

በቤንሻንጉል አሁንም ዜጎችን ማፈናቀሉ ቀጥሏል!

Geez Bet | Wednesday, April 16, 2014
• ‹‹አማራ ክልል አያገባኝም ብሏል››:: 
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት የሚኖሩ የአማራ ብሔር ተወላጆች ለዓመታት ከኖሩበት ቦታ እየተፈናቀሉ መሆኑን ተፈናቃዮች አስታወቁ፡፡ ባለፈው ዓመት ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የአማራ ብሔር ተወላጆች ከክልሉ መፈናቀላቸው የሚታወስ ሲሆን ከሰሞኑ ደግሞ ማፈናቀሉ በአዲስ መልክ የቀጠለ መሆኑ ተመልክቷል፡፡
ተፈናቃዮቹ በክልሉ ድባጤ ወረዳ አልባሳ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ ከ250 ሰዎች በላይ ከአካባቢው ውጡ ተብለዋል፡፡ ‹‹በአካባቢው ሰፈራ እየተሰጠ ነው፡፡ የተባረሩት ሰዎች ግን 15ና 20 አመት በአካባቢው ኖረዋል፡፡ ቤትና ንብረትም አላቸው፡፡ ከጥቅምትና ታህሳስ ጀምሮ ግን ‹እናንተ በአካባቢው መኖር አትችሉም› ተብለው መስፈር የለባችሁም ተብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት እኒህ ሰዎች ዛፍ ስር ነው የሚኖሩት፡፡›› ሲሉ ስለ ሁኔታው ለዝግጅት ክፍላችን አስረድተዋል፡፡
በሌላ በኩል ከወራት በፊት ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉ አርሶ አደሮች አሁንም ድረስ ወደቦታቸው እንዳልተመለሱ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡ በተለይ ህዝቡ ንብረቱን ተቀምቶ ሲባረር በወኪልነት ፌደራል ድረስ መጥተው ህገ-ወጥ ተግባር እየተፈጸመ መሆኑን በማስረዳት ክስ ያቀረቡና አሁንም የተወሰደባቸው ንብረት እዲመለስ የሚከራከሩት ወኪሎች ወደ ቦታቸው መመለስ አለመቻላቸውን አስታውቀዋል፡፡ ለደህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የተፈናቃኞቹ ተወካይ ሲናገሩ፣
ሙሉውን አንብብ-Read More

Gunmen kill nine in western Ethiopia bus attack: state media

Geez Bet | Wednesday, April 16, 2014

ADDIS ABABA (Reuters) - Gunmen ambushed a bus carrying dozens of people in western Ethiopia near the Sudanese border, killing nine and wounding six others, state-run media said on Wednesday.
There was no claim of responsibility and no group was blamed for the attack, but Ethiopia says it has thwarted several plots in recent years by Ethiopian insurgents as well as Somali al Qaeda-linked al Shabaab Islamist militants.
A handful of rebel groups are waging low-level separatist insurgencies in Ethiopia, while Ethiopian troops are part of an offensive against al Shabaab in neighboring Somalia.
The bus ambush on Tuesday evening - near the $4 billion-

ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 15, 2014

በሱሉልታ ከተማ የአማራ ተወላጆች ናችሁ የተባሉ ተደበደቡ

Geez Bet | Tuesday, April 15, 2014
ሶስት ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው በአዲስ አበባ የተለያዩ ሆስፒታሎች ገብተዋል:: 
“ረብሻውን ያነሱት ህዝብን የማይወክሉ ወሮበሎች ናቸው”      የከተማው ኮሙዩኒኬሽን):-


“ባህርዳር በተካሄደው የስፖርት ውድድር ላይ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ አድልዎ ተፈጽሟል” በማለት የተቧደኑ ወጣቶች፣ ባለፈው ሐሙስ የሱሉልታ ከተማ ነዋሪ የሆኑ በርካታ የአማራ ተወላጆች ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ 

በድብደባ በርካታ ሰዎች ከመጐዳታቸውም በተጨማሪ፤ ቤት ንብረት ላይም ጥፋት እንደደረሰ የተናገሩት ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች ጉዳዩን ሕገወጥ ነው ሲሉ አውግዘውታል፡፡ የከተማዋ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ፤ የስፖርት ውድድርን ሰበብ በማድረግ ረብሻ የቀሰቀሱ ሰዎች ህዝብን የማይወክሉ ወሮበሎች ናቸው ብለዋል፡፡ 
ረብሻውን ቀስቅሰዋል ተብለው ከተጠረጠሩት ውስጥ አራቱን በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለም ገልፀዋል ሃላፊው፡፡ 
“የቤቴ በርና መስኮት እንዳልነበር ሆኗል፤ አጥር ተገነጣጥሏል፤ መስኮቶች ዱቄት ሆነዋል”  ያሉት አንድ የከተማዋ የረጅም ጊዜ ነዋሪ፤ ከ30 በላይ ቤቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡   የስድስት ልጆች እናት እንደሆኑ የገለፁልን ሌላዋ ነዋሪ፤ በቤታቸውና በንብረታቸው ላይ አደጋ መድረሱን ጠቅሰው፤ እንደሌሎች ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ባያጋጥማቸውም በእጃቸው ላይ በደረሰባቸው ጉዳት በከተማዋ አንድ ክሊኒክ ህክምና እንደተደረገላቸው ተናግረዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 14, 2014

How History and the 1931 Ethiopian Constitution Perceive the Ethiopians

Geez Bet | Monday, April 14, 2014
This short article addresses the issue of how Ethiopia's social and political problems are sometimes baseless, or based on minor misunderstandings. The Amharic section of the Voice of America (VOA) included a three-part discussion on the history of Ethiopia between Dr. Beyana Soba, a lawyer; Dr. Berhanu Mengist, a
professor of conflict resolutions; and myself, a historian. A historian discussing history with non-historians might seem strange, but the end-result shows that it was actually not. Dr. Beyana represented people who believe that Ethiopian history, as they read it, neither includes them nor respects their human dignity. Dr. Berhanu's place is obvious, as the views of Dr. Beyana and me occasionally conflict. I am satisfied that the discussion took place in this setting because I could hear the complaints of the so-called oppressed people from the source and rebut them. I thank Weyzero Tizzita for conducting the discussions and the VOA for broadcasting them [The discussions are on Ethiopia.org].
The purpose of this note is not to accuse anyone of distorting facts and thereby spoil the friendly atmosphere that prevailed during the discussion. The first misunderstanding came from the reading of the first article of the 1931 Ethiopian Constitution. It reads as follows:

The territory of Ethiopia, in its entirety, is, from one end to the other, subject to the government of His Majesty the Emperor. All the natives of Ethiopia, subjects of the Empire, form together the Ethiopian Empire.
ሙሉውን አንብብ-Read More

Anole Oromo monument and Ethiopia’s history

Geez Bet | Monday, April 14, 2014

 Since the TPLF/OLF created the current ethnic federalism system in 1993, they have brainwashed many Ethiopians to see everything through narrow tribal lense. Therefore, many innocent oromos have become zombies to any tribal propaganda shoved at their throats. Otherwise, the monument has no historical base to support a single brick of its existence!
Why is Anole monument a historical fallacy?
There are three main issues with the monument:
FIRST issue involves the makeup of Menelik’s Shoan army which the OLF/OPDO want us to think are mostly Amharas. But this is completely false. All historical accounts show us that Shoa was a multiethnic region with a significant Oromo population. Even when menelik was imprisoned by the Gojjams, he was helped by the Shoa Oromo to be free and even his wife was mixed Oromo herself. Menelik’s top Minister of Defense was the Oromo/Gurage Commander Habte Dinagde and all of Menelik’s battle with the south was 100% coordinated by Oromo
ሙሉውን አንብብ-Read More

እኩልነት ወይስ የበላይነት? ኢትዮጵያን ለመምታት በማጭበርበር የተገኘ ተራድኦ

Geez Bet | Monday, April 14, 2014
ጌታቸው ኃይሌ :-

መግቢያ፤ 

የዛሬው ድርሰቴ ለመግለጥ የሚሞክረው የዘወትር ድምፃቸው "ተበድለናል" የሚለው፥ የሌላው በደል ግን ደንታቸው 
ያልሆነ፥ የኦሮሞስላሞች አክራሪዎችን ድብቅ ዓላማ ነው። የፈለገ እስላሞሮሞች አክራሪዎች ሊላቸው ይችላል። ዋናው ቁም 
ነገር (1) ኦሮሞ መሆናቸው፥ (2) እስላሞች መሆናቸው፥ (3) አክራሪዎች መሆናቸው፥ (4) የሌላው ነገድ እስላም አክራሪዎች 
የሚደግፏቸው መሆኑ፥ (5) የሚፈልጉት የበላይነት መሆኑ፥ ያ ካልሆነ ኢትዮጵያን ማውደም መሆኑ ለአገር ወዳዱ ሕዝብ 
ግልጽ እንዲሆን ነው። እነሱ ግን "ኦሮሞ" መባልን ይመርጣሉ። ለብልሃታቸው ነው፤ ምክንያቱም፥ ኦሮሞስላሞች ወይም 
እስላሞሮሞች ብቻ መባሉ እውነትነት ቢኖረውም፥ በነጠላው "ኦሮሞ" መባሉ ክርስቲያን ኦሮሞዎችንና እናት አገራቸውን 
የሚወዱ እስላም ኦሮሞዎችን ስለማያካትት፥ የድምፃቸውን ቊጥርና ጉላት በሰሚያቸው ዘንድ ይቀንስባቸዋል። 

የጽሑፌ ርእስና ይዞቱ የሚያመለክተው ይኸንኑ ለማብራራት ነው። ለምሳሌ፥(1) ጨርጨር ውስጥ ባለው በጥንቱ የአሰቦት 
ገዳም ውስጥ በሚኖሩ መነኮሳት ላይ የፈጸሙትን ግድያ የኦሮሞዎች ሁሉ ወንጀል ለማድረግ፥(2) በኦሮሞ ስም ቤተ 
ሙሉውን አንብብ-Read More

ስለፍትህ ሲባል ስርዓቱ ይፍረስ! ፪

Geez Bet | Monday, April 14, 2014
(ተመስገን ደሳለኝ ) :-

 በዚህ ርዕስ ሥር ባለፈው ሳምንት በይደር ካቆየሁት ተከታይ ጽሑፍ በፊት አንድ እርምት የሚያሻው 
ጉዳይን በአዲስ መስመር ላስቀድም፡፡ 

 ሬዲዮ ፋና እና “አምደኞቹ” 

 በ1988 ዓ.ም በኤፈርት ባለቤትነት ስርጭቱን አሀዱ ያለው “ሬዲዮ ፋና”፣ ከምስረታው አንስቶ ዛሬም ድረስ 
ልክ እንደ በረሃው ዘመን ሁሉ የሥርዓቱ ቀኝ እጅና የርካሽ ፕሮፓጋንዳው ማስተላለፊያ ቱቦ ሆኖ መዝለቁ 
ለወዳጅም ለጠላትም የማያከራክር ገሀድ የወጣ ሐቅ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተወሰኑ የግል 

ሚዲያዎች ላይ የርግማን ዘመቻ የታወጀ ይመስል ለተከታታይ ሳምንታት “ስመ-ጥር” ረጋሚዎችን ጣቢያው 
ድረስ ጋብዞ ማብጠልጠልና ማውገዙን ቀንደኛ ሥራው አድርጎ ይዞታል፡፡ በርግጥ ይህ ዘመቻ ከወራት በፊት 
በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና የፕሬስ ድርጅት በኩል በ“ጥናት” ስም የወጣው ውንጀላ ቅጥያ ሲሆን፣ በቅርቡ ኢቲቪ ሰርቶ 
እንዳጠናቀቀው የሚነገርለት ዶክመንተሪ ፊልም ደግሞ “ሳልሳዊ” ዘመቻ ሆኖ ለጥቆ የሚቀርብ መሆኑን የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ 

 ሰሞነኛውን የፋና ዘመቻ ከተለመደው አቀራረብ የተለየ የሚያደርገው ከህወሓት ከበሮ መቺነት መሻገር የተሳነው ዛሚ ሬዲዮ ጣቢያን 
ከወከለው አቶ ዘሪሁን ተሾመ በተጨማሪ፣ የኢዴፓው አቶ ሞሼ ሰሙ እና የ‹‹ፎርቹ››ኑ ጋዜጠኛ ታምራት ወልደጊዮርጊስ በውጋ-ንቀል 
ስልት የርግማኑ ቡራኬ ሰጪ ሆነው መቅረባቸው ነው፡፡ ‹‹አዲስ አማኝ ከጳጳስ በላይ ልሁን ይላል›› እንዲሉ ሩቅ አላሚው የሕዳሴው 
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 13, 2014

ስለፍትሕ ሲባል፤ ሥርዓቱ ይፍረስ!

Geez Bet | Sunday, April 13, 2014
(ተመስገን ደሳለኝ) :-

 ባለፉት አራት አስርታት ሀገሪቱ አያሌ ተግዳሮቶችን መጋፈጧ ባይዘነጋም፤ በተለያየ ጊዜ ሚሊዮኖችን 
ካረገፈው አሰቃቂው ረሃብ በማይተናነስ መልኩ ሕዝቦቿን ዋጋ ያስከፈለ ጉዳይ ቢኖር የፍትሕ አለመከበር 
ያስከተለው ሁለንተናዊ ምስቅልቅሎሽ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስደፍሩ በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ የየካቲቱን

አብዮት ጠልፎ ሥልጣኑን የተቆጣጠረው ወታደራዊው ደርግ፣ የፍርድ ቤት ደጆችን በጓጉንቸር ቆልፎ 
ሲያበቃ፣ የራሱ አባላት እጃቸውን እያወጡ ድምፅ በመስጠት በአፄው ባለስልጣናትንም ሆነ ግብረ-አበሮቹ 
በነበሩ መኮንኖች ላይ የሞት ቅጣትን ያህል የመጨረሻ ከባድ ውሳኔ የማሳለፍን አስደንጋጭ ክስተት ጨምሮ፤  ከከተማ እስከ ገጠር ያደራጃቸው የአብዮት ጠባቂዎችና የገበሬ ማሕበራት ከየቤቱ አንቀው እያወጡ “ነፃ 
እርምጃ” እንዲወስዱ፣ ከየእስር ቤቱ እየለቃቀሙ በጅምላ እንዲረሽኑ በአዋጅ የፈቀደበት ጊዜ የፍትሕ 
ምኩራቡ ፈርሶ በግላጭ የተቀበረበት ዕለት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በርግጥ ይህ የማን-አለብኝነት 
አረመኔያዊ አገዛዝ የታቃውሞውን ጎራ በማጠናከር ታሪካዊ ውድቀቱ እንዲፋጠን ካደረጉ ምክንያቶች አንዱ 
እንደነበር ለመረዳት 17 ዓመታትን መውሰዱ አይዘነጋም፡፡ 

 “ፍትሕ አልባው አምባ-ገነናዊ የደርግ ስርዓት አማርሮ በርሃ ያስወጣንና ብሶት የወለደን የለውጥ ሃዋርያት ነን፤ በመቃብሩም ላይ 
ፍትሕ-ርትዕ የሰፈነባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንመሰርታለ” በማለት ከበሮ ይደስቁ የነበሩት የያኔው “ነፃ አውጪዎች”ም፣ ደርግ አፍርሶ 
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 9, 2014

‹‹ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ካላቆመች ወታደራዊ ኃይል እጠቀማለሁ››

Geez Bet | Wednesday, April 09, 2014
ሞርታዳ ማንሱር፣ የግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዕጩ 
በግብፅ በቅርቡ ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ራሳቸውን በዕጩነት ያቀረቡት የሕግ ባለሙያው ሞርታዳ ማንሱር፣ ‹‹ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ካላቆመች ወታደራዊ ኃይል እጠቀማለሁ፤›› በማለት አስጠነቀቁ፡፡
አወዛጋቢና ስሜታዊ እንደሆኑ በይፋ የሚታወቁት የሕግ ባለሙያና ከሳምንት በፊት ደግም ዛማሌክ ለተባለው ታዋቂ የግብፅ እግር ኳስ ቡድን ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት ማንሱር፣  ማስጠንቀቂያውን ያስተላለፉት ባለፈው እሑድ ፕሬዚዳንታዊ ውድድርን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ላይ ጦነርት በመክፈት የግብፅ ሕዝብን ጥቅም እንደሚያስከብሩም ተናግረዋል፡፡ የዓባይ ወንዝን በተመለከተ እ.ኤ.አ. በ1929 እና በ1959 የተፈረሙ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች መኖራቸውን ያስታወሱት ማንሱር፣ ኢትዮጵያ ይህንን ስምምነት ወደጎን ብላ ግንባታውን መቀጠሏን ተቃውመዋል፡፡

‹‹ኢትዮጵያና ግብፅን ከማግባባት የተቆጠቡ ዓለም አቀፍ ተቋማት አሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ በአቋሟ ፀንታ ግድቡን መገንባት ቀጥላለች፡፡ ኢትዮጵያ ወታደራዊ አቅም እንዳላት በመግለጽ ግብፅን እያስፈራራች ነው፡፡ ነገር ግን ግብፅም ወታደራዊ አቅም አላት፤›› ብለዋል፡፡
ከኢትዮጵያ ጀርባ እስራኤል እንዳለች የተናገሩት ማንሱር፣ ይህ ቢሆንም የግብፅን የውኃ ድርሻ ለመገደብ የሚደረግ ጥረት ለግብፃውያን የሞትና ሽረት ጉዳይ ነው ሲሉ አስታውቀዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 7, 2014

መከላከያ ሚኒስቴር የህዳሴውን ግድብ ከማንኛውም ጥቃት የመከላከል አቅም እንዳለው አስታወቀ

Geez Bet | Monday, April 07, 2014
-ኢትዮጵያና ሱዳን የጋራ ድንበር ጠባቂ ጦር ሊመሠርቱ ነው:: 
የመከላከያ ሠራዊቱ የታላቁ ህዳሴ ግድብንና ሌሎች የአገሪቱ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ከማንኛውም ጥቃት የመከላከል ጠንካራ አቅምና ዝግጁነት እንዳለው፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ለፓርላማ አስታወቁ፡፡ 
አቶ ሲራጅ የመከላከያ ሚኒስቴርን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ባለፈው ሐሙስ ለፓርላማው ባቀረቡበት ወቅት፣ ሠራዊቱ የህዳሴውን ግድብ የመጠበቅ አቅሙና ዝግጅቱ ምን ያህል እንደሆነ እንዲያብራሩ ተጠይቀዋል፡፡ 

ሚኒስትሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ መስጠት የጀመሩት፣ በህዳሴው ግድብ ላይ ሊሰነዘሩ የሚችሉ ጥቃቶች በሁለት መንገድ ብቻ ሊሆኑ እንደሚችሉ በመተንተን ነው፡፡ 
ከተለዩት የጥቃት መንገዶች አንደኛው ቀጥታ በግድቡ ላይ የሚከፈት ቀጥታ ወታደራዊ ጥቃት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች በመጠቀም የሚከፈት ጥቃት ነው ብለዋል፡፡ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ በህዳሴው ግድብ ላይ በቀጥታ የሚፈጸም ጥቃት ይኖራል ብለው እንደማይገምቱ አስረድተዋል፡፡
‹‹አሁን ባለው ሁኔታ በኢትዮጵያ ላይ በቀጥታ የሚሰነዘር ጥቃት ይኖራል ብዬ አላምንም፣ ይከብዳል፤›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ ለዚህ እምነታቸው የተለያዩ ምክንያቶችን አስቀምጠዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ወታደራዊ ባንክ ለመመሥረት የተጀመረው እንቅስቃሴ ተቋረጠ

Geez Bet | Monday, April 07, 2014
የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወታደራዊ ባንክ በማቋቋም በ2006 ዓ.ም. ወደ ሥራ ለመግባት አቅዶ ጀምሮት የነበረውን እንቅስቃሴ አቋረጠ፡፡
የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ባለፈው ዓመት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭና የመከላከያ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት፣ ወታደራዊ ባንክ ለመመሥረት የተጀመረውን እንቅስቃሴ ገልጸው ነበር፡፡ 

ወታደራዊ ባንኩን የመመሥረት እንቅስቃሴው በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል ሲሉ የመከላከያ ሚኒስትሩ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ ባንኩን የመመሥረት እንቅስቃሴ ለምን እንደተቋረጠ ከመግለጽ ተቆጥበዋል፡፡
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጮች ግን ወታደራዊ ባንኩን ለመመሥረት የተጀመረው እንቅስቃሴ የተቋረጠው በብሔራዊ ባንክ ውሳኔ ነው ብለዋል፡፡ 
መከላከያ ሚኒስቴር ወታደራዊ ባንክ ለመመሥረት ከጀመረው እንቅስቃሴ ቀደም ብሎ በተመሳሳይ አነስተኛ የብድርና ቁጠባ ተቋም ለመመሥረት ለብሔራዊ ባንክ የፈቃድ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Apr 2, 2014

ከምዕራብ ሸዋ ዞን መሬት ተቀማን ያሉ የአማራ ተወላጆች ሰሚ አጣን አሉ

Geez Bet | Wednesday, April 02, 2014
“ወደ አንድነት ፓርቲ የመጣነው መሬት ያስመልስልናል ብለን አይደለም” 
 ስምንቱ በአዲስ አበባ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው አድረዋል  
“ያለ አግባብ የተያዘ መሬት ላይ ሁሌም እግድ ይጣላል” - የዞኑ አስተዳደር 
በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ዳኖ ወረዳ አዋዲ ጉልፋ ቀበሌ፤ የመጡ 29 የአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮች “መሬት እንዳናርስ ተከለከልን፤ ቅሬታችንን የሚሰማን አጣን” ሲሉ አማረሩ፡፡ ከ29ኙ ስምንቱ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ፣ ወረዳ ሰባት ፖሊስ ጣቢያ፣ ረቡዕ ማታ ታስረው
ማደራቸውንና ሀሙስ ረፋድ ላይ መለቀቃቸውን አርሶ አደሮቹ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ አብዛኞቹ ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ከጎንደርና ከሌሎች የአማራ አካባቢዎች መሸኛ በማምጣት መሬት እንደተሰጣቸው፣ በአዋዲ ጉልፋ፣ በአጂላ ዳሌና በዙሪያው መሬት በማልማት፣ ቤተእምነት በመገንባትና ሌሎት መሰረተ ልማቶችን በመስራት ከ20 ዓመታት በላይ በሰላም እንደኖሩ ገልፀው፣ ከ2004 ዓ.ም ወዲህ ግን በአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮች ላይ የመሬት እቀባ እንደተጣለ ተናግረዋል፡፡ 
አቶ ቢያዝን አበራ የ65 ዓመት አዛውንት ናቸው። ትውልድና እድገታቸው ጎንደር ቢሆንም በመሬት
ሙሉውን አንብብ-Read More

የአድባራት አስተዳዳሪዎች ማኅበረ ቅዱሳንን በአሸባሪነት መፈረጃቸው ሊቃነ ጳጳሳቱን አስቆጣ

Geez Bet | Wednesday, April 02, 2014
ቅሬታቸውን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች ገልጸዋል
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ በኾኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያኒቱን እምነትና ሥርዐት እንዲማሩ፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን በማቀናጀት ሞያዊ ድጋፍ እንዲያበረክቱ በማስተባበር ላይ የሚገኘውን ማኅበረ ቅዱሳንን በአሸባሪነት በመፈረጅ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካይነት ጠቅላላ ሀብቱና ንብረቱ የሚታገድበት ውሳኔ እንዲተላለፍ በመንግሥትም በኩል እርምትና ርምጃ እንዲወሰድበት የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የአድባራት አስተዳዳሪዎች መግለጫ አውጥተውበታል በተባለው ስብሰባ ጉዳይ ኹለት የቅ/ሲኖዶስ አባላት ለከፍተኛ የመንግሥት ሓላፊዎች ቅሬታቸውን ማሰማታቸው ተገለጸ፡፡

የቅ/ሲኖዶሱን ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሉቃስንና በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስና የጅማ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን በስም የጠቀሱት የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ምንጮች፣ ሊቃነ ጳጳሳቱ ቅሬታቸውን ያቀረቡት ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች እንደኾነ ቢገልጹም የሓላፊዎቹን ስም ከማሳወቅ ተቆጥበዋል። 
ቤተ ክርስቲያኒቱ በፀረ ሙስናና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከመንግሥት ጋራ የተጠናከረ ሥራ ለመሥራት በቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መወሰኗን ሊቃነ ጳጳሳቱ አስታውሰው፣ በዚህም መሠረት ለሙስናና ብክነት
ሙሉውን አንብብ-Read More

የአንድነት አመራሮች በወላይታ ሶዶ እንግልትና የንብረት ውድመት ደረስብን አሉ

Geez Bet | Wednesday, April 02, 2014
 ለውይይት ወደ ወላይታ ሶዶ ሄደው የነበሩት የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አመራሮች  ከፍተኛ እንግልትና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው ገለፁ፡፡ የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ሃላፊና ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊውን ጨምሮ  የፓርቲው የወረዳው አመራሮች ተንቀሳቃሽ ስልኮች ባልታወቀ ኬሚካል ተነክረው ከጥቅም ውጭ መደረጋቸውን የአንድነት ፓርቲ አመራር  አቶ ዳንኤል ተፈራ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ 
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በአንድነት አጠቃላይ እንቅስቃሴና በተሻሻለው የፓርቲው ፕሮግራም ላይ ለመወያየት አቶ ዳንኤል ተፈራና ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ በተደረገላቸው ጥሪ፣  ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ መጓዛቸውን ገልፀው፣ከቀኑ አምስት ሰዓት አካባቢ በአንዱ የአንድነት አባል መኖርያ ግቢ ውስጥ ቡና እየጠጡ ለመወያየት መወሰናቸውን  ይናገራሉ፤ አቶ ዳንኤል ተፈራ፡፡ 

በምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊው የመግቢያ ንግግር ተደርጐ ውይይቱ ሊጀመር ሲል ከስምንት እስከ አስር የሚጠጉ ሰዎች የግቢውን በር በእርግጫ ሰብረው መግባታቸውን ያስታወሱት ሃላፊው፤ሰዎቹ በቀጥታ ፊት ለፊት ያገኙትን እቃ መሰብሰብ መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ሰዎች ታርጋ በሌላቸው ሞተርሳይክሎች እንደመጡ የተናገሩት አቶ ዳንኤል፤ማንነታቸውን እንዳልገለፁ፣ ምን እየሰሩ
ሙሉውን አንብብ-Read More