
Nov 30, 2013
ነገደ ኢትዮጵያ
Geez Bet | Saturday, November 30, 2013

ይህ ጽሑፍ መሪ ራስ አማን በላይ ‹የጥንቷ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ታሪክ› በሚል ርዕስ ከመጽሐፈ ሱባኤ ተረጎምኩት
ብለው በ1985 ዓ.ም. ካሳተሙት መጽሐፍ ከምዕራፍ ሦስት በሙሉ የተወሰደ ነው፡፡ ጽሑፍ እሳቸው እንዳዘጋጁት ነው
እንጂ የተጨመረበት ወይም ኤዲት የተደረገ ነገር የለውም፡፡ መጽሐፉ በያዛቸው መረጃዎችም ሆነ በምንጩ በተለምዶ
ከሚታወቀው የታሪክ መጽሐፎች ይለያል፤ ስለ መጽሐፉ ይዘት፣ ምንጭና አስፈላጊነት ብዙ ማለት ቢቻልም፤ መጽሐፉ ብዙ
ሰዎች በቀላሉ አግኝተውት ያላለነበቡት በመሆኑ አንዱን ምዕራፍ ብቻ እንደነበረ እንደማሳያ ማቅረብ የተሻለ መስሎ
ታይቶኛል፡፡ ለማንኛውም ስለ መጽሐፉ ሁኔታ ለማወቅ በመግቢያውና በመጽሐፉ ጀርባ ከጻፉት ላይ ቀንጭቦ ማየት ጠቀሜታ
ይኖረዋልና እነሆ!
(ከመግቢያው የተወሰደ)
‹‹ይሄን የጥንቷ የኢትዮጵያ ታሪክ ሱዳን አጥባራ በነበርኩበት ጊዜ የኢትዮጵያ...
Nov 29, 2013
አና ጐሜዝ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ገንቢና ግልጽ ውይይቶችን አደረግኩ አሉ
Geez Bet | Friday, November 29, 2013

ከዘጠኝ
ዓመት በፊት በተካሄደው የግንቦት 1997ቱ ምርጫ የአውሮፓ ኅብረትን በመወከል የምርጫ ታዛቢ የነበሩት ፖርቱጋላዊቷ
አና ጐሜዝ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር መነጋገራቸውን ገለጹ፡፡
ዛሬ
በሚጠናቀቀው የአፍሪካ፣ የካሪቢያን፣ የፓስፊክና የአውሮፓ ኅብረት የጋራ የፓርላማ 26ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ
ለመካፈል አዲስ አበባ የመጡት አና ጐሜዝ፣ በአዲስ አበባ በነበራቸው ቆይታ ከኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር
ገንቢና ግልጽ ውይይቶችን ማድረጋቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
የጋራ
ስብሰባው ላይ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ የመጡት የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ አባልና በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ
ከፍተኛ ትችት በመሰንዘር የሚታወቁት አና ጐሜዝ፣ ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ምንም ዓይነት የቪዛ ችግር እንዳልገጠማቸው
ገልጸው ይህም አዲስ ዓይነት...
Nov 29, 2013
የሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና የሙሌት ፖሊሲው
Geez Bet | Friday, November 29, 2013

ጥንታዊ ስልጣኔን ለታሪክ ትተን ከድህነት ወለል በታች ከሚፈረጁት የዓለማችን ኣገራት ተርታ ተሰልፋ የምትገኘው ኢትዮጵያ ግን ደግሞ ይህ ነው የማይባል የተፈጥሮ ሀብትም እንዳላት ይታወቃል።
ከተፈጥሮ ሀብቷ መካከልም ኣንደኛው የውኃ ኃብቷ ሲሆን ወንዞቿ
ደግሞ ድንበር ዘለልም ጭምር ናቸው። ከዚሁ የተነሳ የምስራቅ ኣፍሪካ የውኃ ምንጭ በመባልም ትታወቃለች። ኣንዱና
ዋናው ደግሞ ጥቁር ዓባይ ወይንም በውጪው ኣጠራር ብሉ ናይል ነው። 75 በመቶ
የሚሆነው የናይል ውኃም የሚመጣው...
Nov 26, 2013
የኢራን ሥምምነትና ዉዝግብ
Geez Bet | Tuesday, November 26, 2013

ኢራን ድብቅ የኑክሌር ተቋም እንዳለት ከታወቀበት ከሁለት ሺሕ ሁለት ጀምሮ በቴሕራንና በምዕራባዉያን ሐገራት
ፖለቲከኞችን መካከል የደራዉ ዉዝግብ ለመጀመሪያ ጊዜ-አንድ እልባት አግኝቷል። የእስራኤል-ምዕራባዉያን ልዩነት፥
የኢራን-እስራኤል ዉዝግብስ ነዉ?-የዛሬዉ ጥያቄ
የአያቶላሕ ሩሑላሕ ሆሚኒዋ «ታላቅ ሠይጣን» የድብቅ ዲፕሎማቶች፥ ከጆርጅ ዳብሊዉ ቡሿ «የሰይጣን ዛቢያ» ስዉር
መልዕክተኞች ጋር በዓለም የፖለቲካ መድረክ ብዙም በማትታወቀዉ ሐገር፥ በድብቅ ሆቴል፥ በዘወርዋራ አሳንስር ወይም
ሊፍት ዉስጥ የጀመሩት ድርድር ቅዳሜ-ለዕሁድ አጥቢያ በይፋ ዉል ተቋጠረ።ዤኔቭ።
«ከከባድ ድርድር በሕዋላ ለረጅም ጊዜ፥ አጠቃላይ መፍትሔ በሚያደርሰን የጋራ የድርጊት መረሐ-ግብር ላይ ዛሬ ተስማምተናል።»
የአዉሮጳ ሕብረት የዉጪ ግንኙነት ሐላፊ ወይዘሮ ካትሪን አሽተን።የድብቅ፥ ይፋዉ...
Nov 25, 2013
የሳኡዲ ተመላሾች የስደት መከራቸውን በምሬት ይተርካሉ
Geez Bet | Monday, November 25, 2013

እኛ ተርፈናል፤ እዛ ላሉት ድረሱላቸው ኢትዮጵያውያን ሴቶች ተገደው እየተደፈሩ ነው !እስር ቤት አንዲት ነፍሰ ጡር ሞታብናለች - የስደት ተመላሾች ሳኡዲ
አረቢያ በህገወጥ መንገድ ወደ አገሯ የገቡ ስደተኞችን በሃይል ማስወጣት
ከጀመረች ሁለተኛ ሳምንቷን ያስቆጠረች
ሲሆን ህገወጥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደአገራቸው የመመለስ ዘመቻው አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ ዜጐችን ከሳኡዲ
ለማምጣት ባለፈው ሳምንት በቀን ሰባት በረራዎች ይደረጉ እንደነበር ያስታወሱት የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቃል አቀባይ
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤ በዚህኛው ሳምንት በቀን 12 በረራዎች እየተደረጉ ዜጐችን ማምጣቱ እንደቀጠለና እስከትላንት
ድረስ ከ19ሺ በላይ ዜጐች መመለሳቸውን ገልፀዋል፡፡...
Nov 25, 2013
ኢትዮጵያዊ ዋጋው ስንት ነው?
Geez Bet | Monday, November 25, 2013

(ተመስገን ደሳለኝ)የዚህ ፅሁፍ ማጠንጠኛ የፖለቲካ አመለካከትን መተቸት አይደለም፤ ከዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ወረድ ያሉ የጉልበታሙን ስርዓት የሥራ አፈፃፀሞችን ማብጠልጠልም አይደለም፤ የተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ስንክሳር መንቀስም… አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ (አል-ሀበሽ) መሆን ለፈተና፣ ለመከራ፣ ለሰቆቃ… መዳረጉ የወለደው ብሶት እንጂ፤ መመረር-ማምረር ነው፡፡ …ይህ የእኛ ዕጣ ፈንታ የሆነበትን ምስጢር መመርመር ነው፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
ሰሞኑን የሳውዲ አረቢያ መንግስት ታጣቂዎች እና በድጎማ የሚያድሩ የሀገሬው ተወላጆች በመሰረቱት የጥፋት ግንባር ጉልበታቸውን ገብረው፣ በላብ በወዛቸው በሚያድሩ ስደተኛ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመው አረመኔያዊ ወንጀል፣ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ልብ በከባድ ሀዘን የሰበረ፣ በቁጭት ያንገበገበ አሳዛኝ ፍፃሜ ሆኗል፡፡ ጭፍጨፋው ሃይማኖታዊው...
Nov 24, 2013
አቶ ያረጋል አይሸሹም ከ5 የሙስና ክሶች በ4ቱ ነፃ ሆኑ
Geez Bet | Sunday, November 24, 2013

በተለያዩ ከተሞች በራሳቸው፣ በባለቤታቸውና በልጆቻቸው ስም 17 ቦታዎችንና ቤቶችን ይዘዋል ከሚለው ክስ ነፃ ሆነዋል፡፡
ከባለቤታቸው ጋር ምንጩ ያልታወቀ 490ሺ ብር በባንክ አንቀሳቅሰዋል ከሚለው ክስ ነፃ ናቸው ተብሏል:: የቀድሞው
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ያረጋል አይሸሹም፤ በፀረ ሙስና ኮሚሽን ከቀረቡባቸው አምስት ክሶች
መካከል በአንዱ ብቻ “ጥፋተኛ ናቸው” የተባሉ ሲሆን፣ ምንጩ ያልታወቀ ሃብት አካብተዋል በሚል ከቀረበባቸው ክሶች
ነፃ ሆኑ፡፡
አቶ ያረጋል አይሸሹም እና የትምህርት ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ ሃብታሙ ሂካ፣ ከሁለት የግል
ድርጅት ሃላፊዎች ከአቶ ጌዲዮን ደመቀና ከቶ አሰፋ ገበየ ጋር “ጥፋተኛ ናቸው” የሚል ውሳኔ የተላለፈባቸው፤ ለሦስት
የትምህርት ተቋማት ግንባታ ከወጣው ጨረታ ጋር በተያያዘ ክስ ነው፡፡ ህገወጥ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር ...
Nov 23, 2013
ኢህአዴግ ስለምን ይጮኻል?
Geez Bet | Saturday, November 23, 2013

(ተመስገን ደሳለኝ)በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም በተፈጥሮ ሞት ነውና፡፡ በ1983 ዓ.ም ወርሃ ግንቦት በጠብ-መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ-መራሹ መንግስትም ቢሆን፣ በቀድሞዎቹ ገዥዎች ‹የብረት ጫማ› ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ-ስንብቱን በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል፡፡ ዕ
ለተ-ስንብቱ መቃረቡን የሚጠቁመው ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልክ እንደ ደርግ የመጨረሻዎቹ ወራት ሁሉ፣ ግንባሩና አጋር ፓርቲዎቹ ለየት ባለ መልኩ በራሳቸውና በሹማምንቶቻቸው ላይ በአደባባይ የተቃውሞ ድምፅ ማሰማት መጀመራቸው ነው፡፡ የዚህ ፅሁፍ ተጠየቅም ይህ ነውና ተጨባጭ እውነታውን ለማብራራት በቂ የሆኑ አስረጂዎችን በአዲስ...
Nov 23, 2013
የዓርብ ግዞተኞች
Geez Bet | Saturday, November 23, 2013

አስራት አብርሃም
የሳውዲ መንግስት በወገኖቻችን ላይ እየፈፀመ ባለው ግድያ እና ግፍ ምክንያት በሰማያዊ ፓርቲ የተጠራው ሰልፍ በመንግስት በእኩል ይሁንታ እንዳላገኘ ብንሰማም የሆነው ይሁን እነርሱ በሰው ሀገር መከራና ስቃይ እየተቀበሉ አይደለ በሚል ነው ከተወሰኑ ጓደኞቼ ጋር ወደ ሰልፉ ለመሄድ የቆረጥነው። ችግር ሊኖር እንደሚችል ገምተናል።
ከሰማያዊ ፓርቲ ብርሀኑ ተክለያሬድ ጋር የት ደረሳችሁ እየተባባልን እየተደዋወልን ነበርና በመሀሉ ስልኩ ጠፋኝ። መጨረሻው ግን አራት ኪሎ እንደታገቱ ሰማንና እኔና ሌሎች ሶስት ጓደኞቼ ሆነን ወደ ሰልፉ ቦታ መሄድ ጀመርን። ከኋላችን ብዙ ሰው ቀስ እያለ እየመጣ ነበር። ወደ ሰልፉ እየተጠጋን ስንመጣ ብዙ ሰው ወደእኛ አከባቢ እየሸሸ ሲመጣ ተመለከትን። የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ወጣት ሴት ልጆች እያለቀሱ ወደ እኛ እየመጡ ነው። በዚህ ጊዜ እነ ዳዊት...
Nov 22, 2013
የአፍሪቃና የአውሮፓ የሰብዓዊ መብቶች ውይይት
Geez Bet | Friday, November 22, 2013

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች በአንዳንድ የአፍሪቃ ሃገራት በመገናኛ ብዙሃንና በሰብዓዊ መብት
ተከራካሪዎች ላይ ተጠናክሮ የቀጠለው ጥቃት እንዲቆም እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ብራሰል ቤልጂግ ውስጥ ለተካሄደው
የአፍሪቃና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽኖች የሰብዓዊ መብቶች የጋራ መድረክ አሳስቧል ።
የአፍሪቃ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት በአፍሪቃ ለሰብዓዊ መብት መከበር ለሚታገሉና አውሮፓ ውስጥ ለሚገኙ
የውጭ ዜጎች የተጠናከረ ጥበቃ ለማድረግ በጋራ እንዲሰሩ ተጠየቁ ። የአውሮፓ ህብረትም ለውጭ ዜጎችና ለተገን
ጠያቂዎች የተሻለ ጥበቃ እንዲያደርግ ጥሬ ቀርቦለታል ። ሂሩት መለሰየአፍሪቃ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት ኮሚስዮኖች
ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ ካካሄዱት ዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶች ውይይት ዋነኛ ትኩረቶች አንዱ አፍሪቃ ውስጥ በሰብዓዊ
መብት ተከራካሪዎች...
Nov 21, 2013
የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጤንነት እያነጋገረ ነው
Geez Bet | Thursday, November 21, 2013

- «ፕሬዚዳንቱ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ» አቶ የማነ ገብረመስቀል
- አሜሪካ ዜጎችዋ ወደ ኤርትራ እንዳይጓዙ አስጠነቀቀች
ከመገናኛ ብዙኃንና ከሕዝብ እይታ ከራቁ ከአንድ ወር በላይ የሆናቸው የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጤንነት ጉዳይ እያነጋገረ ነው፡፡
አስማሪኖ
የተባለውና መቀመጫውን በካሊፎርኒያ አሜሪካ ያደረገው የኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚ ድረ ገጽ እንደጻፈው፣ ፕሬዚዳንት
ኢሳያስ ከወትሮው በተለየ ከመገናኛ ብዙኃን ርቀዋል፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ለመጨረሻ ጊዜ በሚዲያ የታዩት ጥቅምት 1
ቀን 2006 ዓ.ም. በተካሄደው የምሥራቅ አፍሪካ የአንበጣ መቆጣጠሪያ ድርጅት የሚኒስትሮች ምክር ቤት 58ኛ ጉባዔ
ላይ መሆኑን ድረ ገጹ ጽፏል፡፡
ከዚያም
በጥቅምት 20 ቀን 2006 ዓ.ም. በጉበት ሕመም ምክንያት አስመራ በሚገኘው...
Nov 21, 2013
የኢትዮጵያውያን ከሳ/አረቢያ መውጣት ያስከተለው ችግር
Geez Bet | Thursday, November 21, 2013

እአአ ከ 610 ዓ ም ጀምሮ የእስልምና ኃይማኖት መገኛ እና ማስፋፊያ ማዕከል በመሆን ትታወቃለች። በማዕከላዊው
ምስራቅ በፋርስ ባህረ ሰላጤ እና በቀይ ባህር መካከል በተንጣለለው የዓረቢያ በረሃ ላይ ጆርዳን ኢራቅ ኩዌት የመን
ኦማን ቀጠር እና የተባበሩት ኣረብ ኢማራት በምድር ያዋስኗታል።
ቀድሞ ኢትዮጵያ ኣሁን ግን ከኤርትራም ጋር የባህር ማዶ ጎረቤት ናቸው። ኣሁን ያለውን ኣገራዊ ቅርጽ ይዛ በኣዲስ
መልክ እንደ መንግስት የቆመችው ከ 1818 ዓ ም ጀምሮ ሲሆን ስያሜዋንም ያገኘችው እ ኣ ዘ ኣ በ 1932 ዓ ም
በንጉስ አብዱልአዚዝ አል ሳዑዲ ኣማካኝነት በንጉሱ የቤተሰብ ስም ተሰይማ መሆኑ ይተረክላታል። ሳዑዲ ዓረቢያ።
በነዳጅ ዘይት ምርቷ በዓለም ቀዳሚነቱን ይዛ የምትገኘው ሳውዲ ኣረቢያ የቆዳ ስፋቷ 2 ሚሊየን ስ ኪ ሜ ገደማ ሲጠጋ
በ2010 በተካሄደ ቆጠራ...
Nov 17, 2013
ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በፀጥታ ሀይሎች ከሸፈ
Geez Bet | Sunday, November 17, 2013

በርካታ ሰዎች ተደብድበዋል በላንቻ ፖሊስ ጣቢያ ከ70 በላይ ሰዎች ታስረዋል
በሳኡዲ አረቢያ በኢትዮጵያዊያን ላይ እየደረሰ ያለውን ግድያና
እንግልት ለመቃወም በትላንትናው እለት ሰማያዊ ፓርቲ ጠርቶት የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በፀጥታ ሀይሎች የከሸፈ ሲሆን፤
ለሰልፉ የወጡት ሰዎች፣ መንገደኞች፣ በተለያየ ምክንያት ጥቁር የለበሱና ሌሎችም ድብደባ ደርሶባቸዋል፡፡ ጋዜጠኞችን
ጨምሮ ከሰባ በላይ ሰዎች በላንቻ ፖሊስ ጣቢያ ታስረዋል፡፡
በድብደባው ሲቪል የለበሱ የፀጥታ ሃይሎችም እንደተጐዱ የላንቻ
ፖሊስ ጣቢያ ሀላፊ ገልፀዋል፡፡ ሰልፉን የጠራው ፓርቲ አመራሮች ከፅፈት ቤታቸው ሳይወጡ መታሰራቸው የተሰማ ሲሆን
የሳኡዲ አረቢያ ኤምባሲ አካባቢ በፌደራል እና በአዲስ አበባ ፖሊስ ተከቦ ውሏል፡፡ ወደ ኤምባሲው የሚጠጋ፣ ሰብሰብ
ብሎ የቆመ፣ ፎቶ ሲያነሳ የተገኘና ሌሎችም በፖሊስ...
Nov 16, 2013
የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት እርማጃና ተቃዉሞዉ
Geez Bet | Saturday, November 16, 2013

አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል።
መንግስት ፈቃድ እንዳልተሰጠዉ በማመልከት ቁጥራቸዉን ባይጠቅስም የታሰሩ መኖራቸዉን ገልጿል። ሰልፉን
ያስተባበረዉ የተቃዉሞ ወገን ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ ሁለት ሊቃነመናብርቱን ጨምሮ አንድ መቶ ሰዎች ገደማ መያዛቸዉን
አመልክቷል። የመንግስት ቃል አቀባይ አቶ ሽመልስ ከማል ፀረ አረብ ስሜት ሊፈጥር የሞከረ ያሉት ተቃዉሞ ሰልፍ
አዘጋጆች ከሚመለከተዉ አካል ፈቃድ ባለማግኘታቸዉ እንደሚከሰሱ ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ ገልጸዋል። በፖሊስ
ከተደበደቡት አንዱ እንደሆነ የገለጸዉ፤ አስፋዉ ሚካኤል መንግስት የሳዉዲ አረቢያን ድርጊት ላይ የቀረበዉን ተቃዉሞ
ለምን ማገድ...
Nov 14, 2013
በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያውያን ስቃይ
Geez Bet | Thursday, November 14, 2013

በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያውያን ስቃይ
ሳዉድ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ዛሬም የድረሱልን ድምጻቸዉን እያሰሙ ነዉ። የሀገሪቱ መንግስት ላለፉት ወራት
ሰጥቶ የቆየዉ የምህረት ቀነገደብ ካለፈ ወዲህ በዜጎችና የጸጥታ ኃይሎች ይፈጸምብናል የሚሉት በደልም ገደብ ማለፉን
ይናገራሉ።
በሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ከ24ዓመታት በላይ እዚያ እንደኖሩ ለዶቼ ቬለ የገለጹት አንድ ዜጋ ደግሞ
ኢትዮጵያዉያኑ ላይ ሀገሬ የሚያሳየዉ ጥላቻ ዛሬ አልተጀመረም ባይናቸዉ። ከያሉበት ታፍሰዉ በመጠለያ ስፍራ
እንደተሰበሰቡ ያመለከቱ ወገኖች ደግሞ ኤምባሲዉ አልደረሰልንም፤ ካለንበት የሚያወጣን አጣን ይላሉ።
ከእነልጆቻቸዉ ታፍሰዉ መጠለያ ከተከተቱ እናቶች አንዷ ናቸዉ። እንባቸዉን እየታገሉ የሚሉት አንድ ነገር
ነዉ፤ ድሃም ብትሆን ሀገር አለን። ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት በርካቶች በአዉቶብስ ያለ...
Nov 14, 2013
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በIMF እይታ
Geez Bet | Thursday, November 14, 2013

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ኣስመልክቶ ላለፉት 9 እና 10 ዓመታት በተለይ ከመንግስት በኩል የሚሰማው እጥፍ ድርብ እድገት
ወይንም በእንግሊዝኛው Double digit grorth ያውም ከ 11 በመቶ ያላነሰ ወይንም ከዚያ በላይ መሆኑ
ይታወቃል። ተቃዋሚዎች በዚያች ኣገር ያንን ያህል እድገት ያውም በኢህኣዲግ የእጅ ኣዙር እዝ ኢኮኖሚ የማይታሰብ ነው
እያሉ
ማጣጣላቸው ባይቀርም የዓለም ባንክ እና ዓለም ዓቀፉ የገንዘብ ተቐም IMF ግን
ሙሉ በሙሉም ባይሆን የመንግስትን የዕድገት ብስራት የሚጋሩት ይመስላል። የመንግስት ባለስልጣናት ለተባለው እድገት
በየዘርፉ እና በየአካባቢው እየተገነቡ ያሉ የመሰረተ ልማት ኣውታሮቶችን እና የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ መሻሻሉን
እንደ ማስረጃ ሲያቀርቡ ተቃዋሚዎች እና ኣንዳንድ ገለልተኛ የሆኑ ባለሙያዎችም እንዲሁ ከወረቀት ኣልፉ መሬት ላይ
ያረፈ...
Nov 13, 2013
Gangrene/ጋንግሪን፡ በደም እጥረት የሞተ የሰውነት ክፍል
Geez Bet | Wednesday, November 13, 2013

ሕመም የትኛውም አካል ላይ ሲከሰት ያሰቃያል። የሕመም
ትንሽ የለውም። ይሁንና አንዳንዴ ሕመምን ከሕመም የማበላለጥ ሃሳብ ይሰጣል። «እንደ ጣት ቁስል አትነ ዝንዘኝ»
የሚለው የጣት ቁስለትን ጥዝጣዜ ያመለክታል። ይህን የጠቀስኩት ብዙውን ጊዜ ከእግር ጣትና እጅ ላይ የሚከሰተውን
ሕመም ምንነት መከላከያና ሕክምና ወዘተ የተመለከቱ መረጃዎችን ለመስጠት አስቤ ነው። – ስለ «ጋንግሪን። ስለ
ጋንግሪን ማብራሪያ የሰጡን ዶክተር ሄለን ይፍጠር ይባላሉ።
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔ ሻሊስት ሐኪምና በስኳር ሕመም ትምህርትና ጥናት ላይ የሚገኙ ምሁር ናቸው።
ጥያቄ፡- ጋንግሪን ምንድን ነው?
ዶክተር ሄለን፡- ጋንግሪን ወደ አማርኛ ሲመለስ በደም እጥረት የሞተ የሰውነት ክፍል እንደማለት ነው። አንድ
የሰውነት ክፍል ደም አጥሮት ምግብና ኦክስጅን አልደርሰው...
Nov 11, 2013
የስዑዲ ምህረትና የሁለት ኢትዮጵያውያን መገደል
Geez Bet | Monday, November 11, 2013

የሳውዲ መንግሥት ለ ሁለተኛ ጊዜ የሰጠው የምህረት አዋጅ ቀነ ገደብ ካበቃበት ካለፈው እሁድ አንስቶ በተካሄደ
የፖሊስ ክትትል ሁለት ኢትዮጵያውያን መገደላቸውን ሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አስታወቁ ። እነዚሁ ነዋሪዎች
እንዳሉት ባለፉት ሶስት ቀናት ከሞቱት ሌላ በርካታ ኢትዮጵያውያን ታፍሰዋል ።
በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ከሞላ ጎደል ሥራቸውን አቁመዋል። የጅዳው ወኪላችን ነበዩ ሲራክ እንደዘገበው የምህረቱ
የመጨረሻ ቀን ካለፈ በኋላ መንግስት በወሰደው እርምጃ ከ 5 ሺህ በላይ የተለያዩ ሃገራት ዜጎች ተይዘዋል።
መንግሥት ሕገወጥ የሚላቸው እነዚህ የውጭ ዜጎች የሁለት ዓመት እሥራትና 100 ሺህ የሳውዲ ሪያል ቅጣት
ይጠብቃቸዋል። ከምህረት አዋጁ ማለቅ በኋላ በጂዳ የኢትዮጵያውያን ዓለም ዓቀፍ ትምህርት ቤት ሥራ መስተጓጎሉንም
ነብዩ ሲራክ ከጅዳ ዘግቧል ።
ነብዩ ሲራክ
ሂሩት...
Nov 5, 2013
አነጋጋሪዉ የስለላ ቅሌትና ጀርመን
Geez Bet | Tuesday, November 05, 2013

የአሜሪካንን ምስጢራዊ መረጃዎች ያጋለጠው የቀድሞው የአሜሪካን የስለላ ድርጅት ባልደረባ ኤድዋርድ ስኖውደን፤ ባለፈዉ
ሳምንት ሐሙስ ከታዋቂዉ የጀርመን ፖለቲከኛ ጋር ሞስኮ ላይ ሲገኛኝ ጀርመን ሁኔታዎችን ካመቻቸችለት በጀርመን ምክር
ቤት ተገኝቶ ስለ አሜሪካ የስለላ ጉዳይ በግልፅ ለመናገር እንደሚፈልግ መናገሩ ይታወቃል።
ይህ ከተሰማ ከቀናቶች በኋላ ደግሞ የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ አርቃቂዎች ለቀድሞዉ የአሜሪካ የስለላድርጅት ባልደረባ
ለኤድዋርድ ስኖዉደን ምንም ዓይነት ምሕረት እንደማይሰጡ ተናግረዋል። የስኖዉደን እና የአሜሪካ ዛቻ የጀርመናዉያን
ለስኖዉደን ጥገኝነት ለመስጠት መፈለግ እያነጋገረ መሆኑን የዶቼ ቬለዉ ፍሪደል ታዉበ ዘግቧል። የአሜሪካንን ምስጢራዊ
መረጃዎች ያጋለጠው የቀድሞው የአሜሪካን የስለላ ድርጅት...
Nov 5, 2013
የራሱን ሚስጥር መጠበቅ ያቃተው የስለላ ድርጅት
Geez Bet | Tuesday, November 05, 2013

በአሜሪካ ስለላ ድፍን አውሮፓ ተናውጧል!
የመከላከያና
የደህንነትን ነገረ ስራ ጉዳዬ ብለው የሚከታተሉ ባለሙያዎች፤ ሰላይና ተሰላይ በአንድ ጣራ ስር አድፍጠው
የየፊናቸውን ጉዳይ የሚከውኑበት መስሪያ ቤቶች ቢኖሩ የስለላ ድርጅቶች ብቻ ናቸው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን እንዲህ
ያለው ሁኔታ ሲያጋጥማቸው ሁሌም የሚጠቀሙበት አንድ አሪፍ አባባል አላቸው፡- “በሬ ካራጁ ይውላል” ይላሉ፡፡
የአሜሪካው
የስለላ ድርጅት ሲአይኤ ይህ አባባል በረጅም የአገልግሎት ዘመኑ ለበርካታ ጊዜ ተጠቅሶበታል፡፡ በተደጋጋሚ ጊዜ
ሌሎችን ለመሰለል የቀጠራቸው ሰላዮቹ፣ ራሱን መልሰው በመሰለል የመከዳትን መራራ ጽዋ ወዶ እስኪጠላ ድረስ ሲግቱት
ኖረዋል፡፡
ኤንኤስኤ በሚለው አጭር ስያሜው ይበልጥ የሚታወቀው ብሔራዊ የደህንነት ድርጅት አሜሪካ ካሏት የተለያዩ የመረጃና የደህንነት ድርጅቶች አንዱ ነው፡፡...
Nov 4, 2013
የ“ኢትዮ - ምህዳር” ጋዜጠኛ ከደረሰበት አደጋ ከሞት ተርፏል
Geez Bet | Monday, November 04, 2013

ለቀጣይ ህክምና 60ሺህ ብር ተጠይቋል
ጋዜጠኞች ገንዘብ ለማሰባሰብ መክረዋል
ከተመሰረት ጥቂት ወራትን
ያስቆጠረው የ “ኢትዮ-ምህዳር” ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ ሚሊዮን ደግነው፣ ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ወርቁ እና አዘጋጁ
ኤፍሬም በየነ ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ወደ ሀዋሳ የተጓዙት ለሽርሽር አልነበረም። በነጋታው ረቡዕ የፍ/ቤት ቀጠሮ
ስለነበራቸው ነው፡፡
ከሁለት ሳምንት በፊት “ኢትዮ-ምህዳር”፤ ከሙስና ጋር በተያያዘ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዙሪያ
በዘገበው ዜና ምክንያት፣ ዩኒቨርስቲው በጋዜጠኞች ላይ የ300ሺ ብር ክስ እንደመሰረተባቸው ይታወሳል። ጋዜጠኛ
ኤፍሬም አብሯቸው የተጓዘው አንድም ዜናውን የሰራው እርሱ በመሆኑ፣ ተከራከሩ ቢባል ለፍ/ቤቱ በደንብ እንዲያስረዳ፣
ሁለትም የተከሳሽ ባልደረቦቹን የፍርድ ቤት ውሎ በአካል ተገኝቶ ለመዘገብ እንደነበር ዋና አዘጋጁ ጌታቸው ወርቁ
ተናግሯል፡፡...
Nov 4, 2013
ንግስት ሳባ አረብ ሳትሆን ኢትዮጵያዊት ንግስት ናት!
Geez Bet | Monday, November 04, 2013

በታላቁ መጽሃፍ “መጽሃፍ ቅዱስ” ላይ በመጽሃፈ ነገስት ቀዳማዊ ላይ በምዕራፍ 10 ከቁጥር 1 እስከ 13 ድረስ
ንግስተ ሳባ ጠቢቡ ሰለሞንን ጎብኝታ ወደ ሃገሯ እንደተመለሰች ይናገራል፡፡ ዓረቦች ይህንን ታሪክ የግላቸው ለማድረግ
መጠነ ሰፊ ጥረት አድርገዋል፤ ባይሳካላቸውም፡፡
ንግስተ ሳባ የራሳቸው ንግስት በመሆን ጠቢቡን ጎብኝታ ለመመለሷ
እንደ ማስረጃ የሚያነሱት በዓረቦች ውስጥ የሳባ ዓረቦች የሚባሉ ነገዶች ነበሩና የነሱም መጠሪያ ይህችው ሳባ ናት
በማለት ነው፤ የርሷም መነሻ ዓረብ ነው በማለት፡፡ “ንግስተ ሳባ የኛ የሃገራችን ንግስት ሆና ጠቢቡ ሰለሞንን
ለማየት ወደ ኢየሩሳሌም ከኢትዮጵያ ሳይሆን ከሃገራችን ተነስታ ሄደች፡፡” የሚልም በመጽሃፋቸው “በቁርዓን ሲራ 27”
ላይ ሰፍሯል፡፡ የኛ ኢትዮጵያኖች ደግሞ “አይደለም ተሳስታችኋል… ንግስተ ሳባ ኢትዮጵያዊት...
Nov 4, 2013
የጉዲፈቻ ልጃቸውን የገደሉ ተፈረደባቸው
Geez Bet | Monday, November 04, 2013

ኣንዲት የጉዲፈቻ ልጃቸውን ኣሰቃይተው ለሞት ያበቁ ባልና ሚስት አሜሪካውያን ከ28 እስከ37 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተፈረደባቸው።
የ13 ዓመትዋ ሐና ዊሊያምስ ህይወቷን ያጣችዉ በጎርጎሪዮሳዊዉ የዘመን ቀመር ግንቦት 12 ቀን 2011
ሲሆን ከትናንንት በስተያ ማክሰኞ ዕለት ያስቻለው የሲኣትል ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ ሚስት ወ/ሮ ካሪ ዊሊያምስ
37 ዓመት እና ባል ላሪ ዊሊያምስ ደግሞ 28 ዓመት እንዲታሰሩ ፈርዶባቸዋል።
ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ኣንድ ሌላ እትዮጵያዊ የጉዲፈቻ ልጅን ጨምሮ ሰባት አብራካቸዉ የተገኙ ልጆችም ኣሏቸው።
በ ዩኤስ አሜሪካ ከሴኣትል በስተ ሰሜን 60 ማይልስ ወይንም 100 ኪ ሜ ላይ በምትገኘው መለስተኛ
ከተማ ሲድሮ ዊሊ ነዋሪ የሆኑት ካሪ ዊሊያምስ እና ባለቤትዋ ላሪ ዊሊያምስ የራሳቸው 7 የአብራክ ልጆች እያላቸው
ከእነዚህ በተጨማሪ...
Nov 4, 2013
የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች
Geez Bet | Monday, November 04, 2013

የጋራ ማሕበር ለመመስረት የተስማማሙት ፖለከኞች እንደሚሉት የመጨረሻ አላማቸዉ ቢቻል ሁሉንም በሰላማዊ መንገድ
የሚታገሉ ተቃዋሚዎችን ይሕ ቢቀር ሰላሳ ሰወስት ፓርቲዎችን አስተባብሮ አንድ ጠንካራ ተቃዋሚ ጎራ ለመፍጠር ነዉ።ይሕ
ምናልባት ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት በተቃዋሚዉ ጎራ የሚታየዉን መከፋፋል፥ መሰነጣጠቅና መጠላለፍ ለማስቀረት ይረዳ
ይሆን?
አስር የሚሆኑ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የጋራ ማሕበር ወይም ቅንጅት ለመመሥረት ተስማምተዋል። አደራጆቹ እንደሚሉት አሁን የጋራ ሕብረት የሚመሠርቱት ፓርቲዎች በሒደት በርካታ ፓርቲዎችን
ከሚያስተናብረዉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ መድረክ ጋር የጋራ ትብብር ወይም ሕብረት የመመስረት እቅድ
አላቸዉ።የጋራ ሕብረት ከሚመሠርቱት መካከል ደግሞ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት...