
Mar 26, 2014
የደቡብ ሱዳንና የግብፅ ወታደራዊ ስምምነት
Geez Bet | Wednesday, March 26, 2014

ደቡብ ሱዳን ከግብፅ ጋ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብር ስምምነት መፈራረሟን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ጁባ ተመሳሳይ መግባባት ላይ ከሁለት ዓመታት በፊት ከተነጠለቻት ሰሜን ሱዳን ጋም መድረሷ ተገልጿል።
ሱዳን ትሪቢዩን እንደሚለዉ የደቡብ ሱዳን እና ግብፅ ወታደራዊ ትብብር መፈራረም ይፋ የተደረገዉ በጁባ መንግስት ሥር
በሚተዳደረዉ የደቡብ ሱዳን ቴሌቪዥን ነዉ። በመከላከያ ሚኒስትር ኩሎ ማንያንጋ ጁኩ የሚመራ የደቡብ ሱዳን የልዑካን
ቡድን ካይሮን በጎበኘበት ወቅት ነዉ ካይሮና ጁባ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብር ስምምነቱን የተፈራረሙት። ዝርዝር
ስምምነቱ ይፋ ባይሆንም የዜና አዉታሩ ወታደራዊ ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበዉ የወታደራዊ ኃይሎች የልምድ ልዉዉጥ፣
ልዩ ኃይሎችን የማሰልጠን እና በጋራ ልምምዶችን ማድረግን ያካትታል። ግብፅም ሆነች ደቡብ ሱዳን አሁን በሚገኙበት
ያልተረጋጋ...
Mar 26, 2014
የሙሥሊም ወንድማማቾች የሞት ብይን
Geez Bet | Wednesday, March 26, 2014

በትናንትናዉ ዕለት የግብፅ ፍርድ ቤት በ529 የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር አባላት ላይ የሞት ቅጣት በይኗል።
ዉሳኔዉ በተሰጠበት በዚሁ ችሎት 147ቱ ብቻ ናቸዉ በስፍራዉ ተገኝተዉ ፍርዱን ያደመጡ ሲሆን ቀሪዎቹ ከሚጠብቃቸዉ
ፍርድ ለማምለጥ በሽሽት ላይ መሆናቸዉ ተገልጿል።
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የካይሮ መንግስት የሞት ፍርድ ዓለም ዓቀፍ ሕግን እንደ ሚፃረር በማሳሰብ፤ ሌሎች
ተመሳሳይ እጣ ይጠብቃቸዋል ያላቸዉ በሺዎች የሚገመቱ ዜጎች ሁኔታ እንደሚያሳሰበዉ ዛሬ አስታዉቋል።
ትናንት ግብፅ ዉስጥ የተላለፈዉ የሞት ቅጣት ብይን በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ የመጀመሪያዉ መሆኑ ነዉ የተገለጸዉ።
ብይኑ ሲሰጥ ፍርድ ቤት በአካል የቀረቡት 147ቱ ሲሆኑ ቀሪ 398ቱ በሌሉበት ነዉ የተበየነባቸዉ። የእያንዳንዱ
የክስ ሁኔታ ባለመነበቡም ማን በምን ምክንያት የሞት ብይን...
Mar 24, 2014
የብሔራዊ ፈተናዎች ኩረጃ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ በጥናት ተመለከተ
Geez Bet | Monday, March 24, 2014

የአገሪቱ ብሔራዊ ፈተናዎች ላይ የሚታየው ኩረጃ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ጥናት ተጠቆመ፡፡ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም.
‹‹በብሔራዊ ፈተናዎች ዙሪያ የሚስተዋሉ የሥነ ምግባር ችግሮች፣ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎቻቸው›› በሚል ርዕስ ኮሚሽኑ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የቀረበው የመነሻ ጥናት ችግሩ አሳሳቢ ነው ተብሏል፡፡
የአገሪቱን የነገ ዕጣ የሚወስኑና ችግር ፈቺ ይሆናሉ የሚባሉ ተማሪዎች በተደራጀ ሁኔታ ኩረጃ ላይ መትጋታቸው
ከሥነ ምግባር ችግርነት አልፎ በሙስና የሚፈረጅበት ደረጃ ላይ መድረሱን፣ በኮሚሽኑ የሥነ ምግባር ትምህርት ባለሙያ
በመሆን ለአሥር ዓመታት ያገለገሉትና የጥናቱ አቅራቢ የሆኑት አቶ ከበደ ሲማ ገልጸዋል፡፡ ችግሩ አሳሳቢ ደረጃ ላይ
በመድረሱ እንደ አገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና...
Mar 24, 2014
የግብፅ ኩባንያ በኢትዮጵያ ትልቁን የወርቅ ክምችት አገኘ
Geez Bet | Monday, March 24, 2014

አስኮም ማይንኒግ የተባለው የግብፅ ኩባንያ በኢትዮጵያ ታሪክ እስከዛሬ ከተገኘው የላቀ የወርቅ ክምችት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አገኘ፡፡
የተገኘው የፅንስ ወርቅ ክምችት በኢትዮጵያ የወርቅ ፍለጋ ታሪክ ከተገኙ የወርቅ ክምችቶች በሙሉ ይበልጣል ተብሏል፡፡
በቅርቡ ከተደረሰባቸው የወርቅ ክምችቶች መካከል በቱሉ ካፒ ወለጋ ኒዮታ ሚኒራልስ የተሰኘ የእንግሊዝ ኩባንያ፣
በመተከል ሳካሮ በሚድሮክ ጐልድ በኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች በናሽናል ማይኒንግ በአፋርና በትግራይ ክልሎች ስትራቴክስ
በተባለው የእንግሊዙ ኩባንያ፣ በትግራይ ክልል በኢዛና ማይንኒግ የተገኙት ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የግብፅ ኩባንያ
አስኮም በቤኒሻንጉል
ጉሙዝ ክልል ያገኘው የወርቅ ክምችት በእነዚህ ኩባንያዎች ከተገኙት ክምችቶች ሁሉ እንደሚበልጥ
ተገልጿል፡፡
የማዕድን...
Mar 22, 2014
Group: Ethiopia Regularly Records Phone Calls
Geez Bet | Saturday, March 22, 2014

NAIROBI, Kenya (AP) — A rights group says that Ethiopia's government
regularly listens to and records the phone calls of opposition activists
and journalists using equipment provided by foreign technology
companies.
Human Rights Watch said in a report Friday that the foreign equipment
aids the Ethiopian government's surveillance of perceived political
opponents inside and outside the country.
The group's Arvind Ganesan said Ethiopia is using its
government-controlled...
Mar 18, 2014
የክሪሚያ ሕዝበ ዉሳኔና አፀፋዉ
Geez Bet | Tuesday, March 18, 2014

ጊዚያዊ ጥቅላይ ሚንስትሩ እንዳሉት የሩሲያ ጦር በሳቸዉ አገላለጥ ለክሪሚያ «ገንጣይና ከፋፋዮች» ከለላ መስጠቱ
እዉነት ነዉ።የዚያኑ ያክል ያዜንዩክና ጓዶቻቸዉ በዩናይትድ ስቴስና በተባባሪዎችዋ እቅፍ ዉስጥ መሆናቸዉም ሐቅ።
የኪየቭ-አዲስ መሪዎች የትንሽ ግዛታቸዉን ትንሽ ጠላቶቻቸዉን ትተዉ የትልቅ ጎረቤታቸዉን ትልቅ ጠላታቸዉን እያወገዙ ደግሞ በተቃራኒዉ እንደራደር ይላሉ።የበርሊን-ለንደን-ፓሪስ መሪዎችና ተከታዮቻቸዉ ኪየቮችን ለፍጥጫ እያጃገኑ፤ ሞስኮዎችን ለመቅጣት እየዛቱ ከኪየቮች ጋር ተወያዩ ይላሉ።ኪየቭ-ብራስልሶችን የሚመሩት የዋሽግተን መሪዎች ሞስኮዎችን የሚያስፈራራ ጦር እያዘመቱ፤ ሞስኮዎችን እየቀጡ፤ ለተጨማሪ ቅጣት እየዛቱ ከሞስኮዎች ጋር ይደራደራሉ።የሞስኮ ጠላቶች የሌሉ ያክል የዘነጓቸዉ የክሪሚያ የሞስኮ ታማኞች ትንሺቱን፤ ጥንታዊቱን ሥልታዊ ግዛታቸዉን ለሞስኮዎች...
Mar 17, 2014
ግብረሶዶማዊነትን ለምን እንቃወማለን?
Geez Bet | Monday, March 17, 2014

(ካሣሁን ዓለሙ):-
አንዳንድ ጊዜ የግብረ ሰዶማዊነት የዚህን ያህል አሟጋች መሆኑን ሳይና በአለማቀፍ ተቋማት ድጋፍ አግኝቶ
እንዲስፋፋ ሲደረግ ስመለከትና ስሰማ ይገርመኛል፤ ግርምቴ ዝም ብሎ የመጣ አይደለም፤ ይልቁንም ግብረሰዶም ከሰው
ልጆች ተፈጥሮ ውጭ የሆነ ተግባር መስሎ ስለሚታየኝና የሚሰጠው ጥቅም አልገለጽልህ ቢለኝ ነው፡፡ ስለዚህ የራሴን
መሟገቻ ነጥቦች ላቅርብ ፈለግሁ ይህ ጽሑፍም በዚህ ዕይታ የተቃኘ ነው፡፡ መልካም ንባብ!
ለመሟገትም ‹ግብረሰዶማዊነት ተፈጥሮ የሚደግፈው ድርጊት ነው ወይ?› በሚል ጥያቄ መነሣት የግድ ይላል፤ መልሱም
‹ግብረሰዶማዊነት ተፈጥሯዊ ነው› የሚል ከሆነ...
Mar 17, 2014
‹‹ለእኔ የአካዳሚክ ነፃነት ችግር ሆኖ አያውቅም›› ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ
Geez Bet | Monday, March 17, 2014

ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ፣ የኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትና ተገቢነት ተመራማሪ
ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ የተወለዱት አስመራ ነው፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን አስመራ፣ የሁለተኛ ደረጃን ደግሞ በጅማ ነው የተከታተሉት፡፡
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአስመራ ዩኒቨርሲቲ በሕግ አግኝተዋል፡፡ ለሁለት ዓመታት ከሠሩ በኋላ ስኮላርሺፕ
አግኝተው እንግሊዝ ከሄዱ በኋላ ለረዥም ዓመታት ቆይተዋል፡፡ ያጠኑት ታሪክ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትና
ተገቢነትን በተለያዩ ጥናቶቻቸው ለሃያ ሦስት ዓመታት ተመልክተዋል፡፡ “Crisis of Ethiopian
Education፡ Implications for nation Building, Rethinking Ethiopian
Education, Ethiopian Education from Crisis to Collapse” በሚሉ ርዕሶች መጻሕፍትም
አሳትመዋል፡፡...
Mar 15, 2014
“ቅዱስ ኤልያስ ይዞት የመጣውን መፅሐፍ” ቤተ ክርስትያን እንድትቀበል ተጠየቀ
Geez Bet | Saturday, March 15, 2014

መጽሐፉ ለአቡነ ማትያስና ለጠ/ሚ ኃይለማርያም እንዲደርሳቸው ተደርጓልደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠ/ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታናሁ እና ለተመድ ተልኳል
ከተፃፈ ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ አስቆጥሯል የተባለውንና ስለ ቅዱስ ኤልያስ መምጣት ምስጢር የሚተነትነውን መጽሐፍ፣
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተቀብላ ወደተለያዩ ቋንቋዎች በማስተርጎም ምዕመናኖችን እንድታስተምር፣
“ማህበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ለቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በጻፈው ደብዳቤ ጠየቀ፡፡...
Mar 13, 2014
የአ.አ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ የትምህርት ዘርፍና ፈተናው
Geez Bet | Thursday, March 13, 2014

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ የትምህርት ክፍል በተማሪዎች ብዙም የማይመረጥበት ሁኔታ የትምህርት ዘርፉን ሕልዉና ሳይፈታተን እንደሚይቀር እየተገነገረ ነዉ።
ወደዩኒቨርሲቲ የመግባት እድል ከሚያገኙ ተማሪዎች አብዛኞቹ ከምረቃ በኋላ ሥራ ከማግኘት እድል ጋ በተያያዘ
የትምህርት ዘርፉን ከመምረጥ ሲቆጠቡ፤ 70/30 የተሰኘዉ የትምህርት ፖሊሲም የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረጉን ታዛቢዎች
ያመለክታሉ። እንዲያም ሆኖ ከዘርፉ ምሁራን አንዳንዶች በቀጣይ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ሕልዉናዉ ተጠናክሮ ይቀጥላል
የሚል ተስፋ አላቸዉ።
በቅርቡ ነዉ የታሪክ የትምህርት ክፍል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተከፈተበትን 50ኛ ዓመት ያከበረዉ። በወቅቱም
በያዝነዉ የትምህርት ዓመት በትምህርት ክፍሉ ለመማር የተመዘገበ ተማሪ አለመኖሩ ተገልጿል። ለዚህ እንደምክንያት...
Mar 10, 2014
ፓትርያርኩ ‹‹ቤተ ክርስቲያን በዩኒቨርስቲ ምሩቃን አትመራም” ማለታቸው ቅሬታ ፈጠረ
Geez Bet | Monday, March 10, 2014

ስለማኅበራት የሰጡትን አስተያየት መልሰው እንዲያጤኑት ተጠየቀ ‹‹ማኅበራት በትኩረት ሊመሩና ጉዟቸውም እየተፈተሸ ሊስተካከል ይገባል›› - መንግሥትየኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ‹‹ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው ቤተ
ክርስቲያንን እንምራ እያሉ ነው፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ትውፊትና ሥርዓት አላት፤እንዲህ ማለት አይችሉም›› በማለት
የሰጡትን አስተያየት መልሰው እንዲያጤኑት በንግግራቸው ቅር የተሰኙ የመንፈሳውያን ማኅበራት አገልጋዮች ጠየቁ፡፡አገልጋዮቹ
ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፣ አቡነ ማትያስ ይሄን አስተያየት የሰነዘሩት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ
ክህነት ጽ/ቤት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ከኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ጋር በመተባበር
የካቲት 21 እና 22 ያዘጋጁት ሀገር አቀፍ የስብከተ ወንጌል...
Mar 10, 2014
ተራማጁ ደራሲ ለምን ተገለለ?
Geez Bet | Monday, March 10, 2014

የፈጠራ ስራዎች ፀረ-ፊውዳል ድርሰቶች አይደሉም የሚል ምሁር ከመካከላችን ይኖራል? ታዲያ ፀረ-ፊውዳል ታጋዩና
የመሬት ላራሹ መፈክር አንጋቢው ተራማጁ የተማሪዎች ማህበር ይህን ህዝባዊ ደራሲ ሳያጎላው ያለፈው ሆን ብሎ ይሆን
ወይስ ረስቶት?ይህን ጽሑፍ ያዘጋጀሁት ስለ አንጋፋው ደራሲ አቤ ጉበኛ አንዳንድ ሃሳቦችን ለመሰንዘር
ነው። ጽሑፉ ከምርምርም በሉት ከጥናት ሥራ ጋር የሚመደብ አይደለም፡፡ ወፍ በረር ወይም ወፍ ዘለል ምልከታ
አይባልም፡፡ በአጭሩ እኔ ስለአቤ የተሰማኝን የገለጽሁበት መላምታዊ ስሜት ነው፡፡ አቤን እኔ በሚገባ ወይም
በቅርበት አላውቀውም፡፡ የአቸፈር ሰው መሆኑን፣ ዳንግላ መማሩን የተረዳሁት በቅርቡ ነው፡፡ የእኛ ዘ...
Mar 10, 2014
አንድነት ሁለተኛውን ዙር “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት”ንቅናቄ ጀመረ
Geez Bet | Monday, March 10, 2014

የመሬት ፖሊስን ለማስለወጥ እታገላለሁ ብሏል አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የመሬት ጥያቄን አጀንዳው
በማድረግ ለሶስት ወራት የሚዘልቅ ሁለተኛ ዙር “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” ንቅናቄ መጀመሩን ጠቁሞ መሬት
በመንግስት ቁጥጥር ስር መሆኑን በመቃወም እንደሚንቀሳቀስ ገልጿል፡፡ፓርቲው በትናንትናው እለት በሠጠው ጋዜጣዊ
መግለጫ፤መሬት በመንግስት ቁጥጥር ስር መዋሉን በመቃወም የፖሊሲ ለውጥ እንዲደረግ ጫና ለመፍጠር፣ አዲስ አበባን
ጨምሮ በተመረጡ 14 የክልል ከተሞች ህዝባዊ ስብሠባ የሚያካሂድ ሲሆን ስብሠባዎቹ በደሴ እና
በድጋሚ በአዲስ አበባ የሚደረግ ሲሆን በየ15 ቀን ልዩነት በሃዋሣ፣ አዳማ፣ ለገጣፎ፣ መቀሌ፣ ደብረታቦር፣ ደብረ
ማርቆስ፣ ድሬዳዋ፣ ጂንካ፣ ቁጫ፣ አሶሣ፣ ነቀምት እና ጋምቤላ ከተካሄደ በኋላ አዲስ አበባ ላይ በሚደረግ...
Mar 10, 2014
The art of ancient writing
Geez Bet | Monday, March 10, 2014

The Nephilim were offspring of
the “sons of God” and the “daughters of men”. According to records, with
the fall of the Watchers, the angels who fathered the Nephilim, a
phenomenon was created in the world.
“They became pregnant, and they
bore great giants, whose height was 35 meters and who consumed all the
acquisitions of men. And when men could no longer sustain them, the
giants turned against them and devoured humankind”. This text was taken
from the book of Enoch (Metshafe...
Mar 5, 2014
የዩክሬን ቀውስ፣ የአውሮፓ ህብረትና የሩስያ ግንኙነት
Geez Bet | Wednesday, March 05, 2014

ትናንት ብራሰልስ ቤልጅየም የተሰበሰቡት የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሩስያ ጦሯን ከዩክሬን ካላስወጣች
ከሩስያ ጋር የተጀመረው ንግግር እንደሚቋረጥ እንዲሁም ማዕቀቦች እንደሚጣሉባት አስጠንቅቀዋል ።
«አውሮፓ የበርሊኑ ግንብ ከፈረሰ ወዲህ ያለ አንዳች ጥርጥር እጅግ ከባድ ቀውስ ውስጥ ትገኛለች ። ቀዝቃዛው ጦርነት ካበቃ ከ25 ዓመት በኋላ የአውሮፓ አዲስ የመከፋፈል አደጋ እውን ሆኗል »
የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ትናንት በዩክሬን ቀውስ ላይ የተነጋገረው የአውሮፓ
ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አስቸኳይ ስብሰባ ከመጀመሩ አስቀድሞ የሰጡት አስተያየት ነበር ። በርግጥም
ሽታይናማየር እንዳሉት አውሮፓ ከባድ ችግር ውስጥ ነው ያለችው ። በአንድ በኩል በእጇ...