
Feb 26, 2014
<< የፀረ ግብረ ሰዶማዊ ሕጐችን ማውጣት የመንግሥታት ሥራ አይደለም>> ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ
Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014

በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ የሰፈረው መልዕክት አነጋጋሪ ሆኗል!
-መንግሥት አካውንታቸው ተጠልፏል እያለ ነው::
የሴቶች፣ የሕፃናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በትዊተር ማኅበራዊ ገጻቸው ላይ፣ ‹‹በተወዳጇ አፍሪካዬ ውስጥ ጥላቻና መገለል ቦታ የላቸውም፡፡
የአለባበስ
ሥርዓት ወይም የፀረ ግብረ ሰዶማዊ ሕጐችን ማውጣት የመንግሥታት ሥራ አይደለም፤›› በሚል የወጣው መልዕክት
አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ መንግሥት ግን የሚኒስትሯ የትዊተር አካውንት መጠለፉን ገልጾ፣ ይህ መልዕክት የሚኒስትሯንም ሆነ
የመንግሥትን አቋም አይወክልም ሲል አስተባብሏል፡፡
በዚህ
ሳምንት መጀመሪያ ላይ በኡጋንዳ የፀደቀውን ፀረ ግብረ ሰዶማዊያን ሕግ በመቃወም በሚኒስትሯ የትዊተር ገጽ ላይ
የተጻፈው ይህ መልዕክት፣ በዓለም ዙሪያ ባሉ የግብረሰዶማዊ...
Feb 26, 2014
ዩጋንዳና ግብረ ሰዶማዊነትን የሚቃወው ህጓ
Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014

በዩጋንዳ ትናንት ጀምሮ ግብረ ሰዶማዊነት የሚቃወም ህግ ተደንግጓል ። የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የዩጋንዳ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግብረ ሰዶማዊነትን በመቃወም ባለፈው ታህሳስ ያሳለፈውን ህግ ትናንት በፊርማቸው
አፅደድቀዋል ። ህጉ የፀደቀው በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና ግብረሰዶማዊነትን በሚቃወሙ ወገኖች መካከል
ለዓመታት ከተካሄደ ትግል በኋላ ነው ። በአዲሱ ህግ የሰዶማዊነት ተግባር በእድሜ ልክ እሥራት ያስቀጣል ። አዲሱ ህግ ከመፅደቁ በፊት ብዙ ጊዜ ወስዷል ።
እጎአ በ2009 ነበር ግብረ ሰዶማዊነትን የሚቃወም ረቂቅ ህግ ለዩጋንዳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ።
የያኔው ረቂቅ ህግ በተደጋጋሚ የግብረ ሰዶም ተግባር ሲፈፅም በተገኘ ሰው ላይ እስከ ሞት ቅጣት የሚደርስ ብይን
እንዲተላለፍ የሚደነግግ ነበር ። ይህም በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ ።...
Feb 26, 2014
በኑሮ መማረሩን ተናግሯል የተባለው የጥበቃ አባል ራሱን አጠፋ
Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014

በቦሌ
ዋናው መንገድ ከሚሊኒየም አዳራሸ ማዶ በሚገኘው የሕብረት ባንክ አክሲዮን ማኅበር ቅርንጫፍ በጥበቃ ሥራ ላይ
የተሰማራው ወጣት፣ ‹‹ኑሮ መሮኛል›› በማለት እየተናገረ ለጥበቃ በያዘው ጠመንጃ የካቲት 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
ከሰዓት በኋላ ራሱን አጠፋ፡፡
ወጣቱ
የጥበቃ ሠራተኛ በሱፈቃድ በጋሻው በኪሱ ውስጥ ከተገኙት የተለያዩ መታወቂያዎች መረዳት እንደተቻለው፣ አጋር የጥበቃ
ሠራተኞች ማሠልጠኛ ተቋም ተቀጣሪ ነው፡፡ በተጨማሪም የኮሌጅ ተማሪ መሆኑን በሚገልጸው መታወቂያ ላይ እንደሠፈረው
ከሆነ፣ በ1982 ዓ.ም. የተወለደና የ24 ዓመት ወጣት ነው፡፡ በምን ምክንያት ከፖሊስ ባልደረባነት እንደለቀቀ
ባይታወቅም፣ የ13ኛ ኮርስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባል እንደነበር በቅርብ ከሚያውቁት ወዳጆቹ ለማወቅ
ተችሏል፡፡
በባንኩ
አሠራር አንድ የጥበቃ አባል 24...
Feb 26, 2014
ግብፅ በህዳሴው ግድብ ላይ የጀመረችውን ዘመቻ ዓለም አቀፍ ገጽታ ልታላብሰው ነው
Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014

-ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከነካቢኔያቸው ሥልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ
የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ የጀመረውን ዘመቻ ዓለም አቀፍ ገጽታ ለማላበስ አዲስ እንቅስቃሴ ሊጀምር ነው፡፡
ከወደ ግብፅ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የግብፅ የውኃና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ይህንን አዲስ እንቅስቃሴ ያስተባብራሉ፡፡
ከዚህ
ቀደም ግድቡን በተመለከተ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ፀጥታው ምክር ቤት አቤቱታ ለማቅረብ የተጀመረው
እንቅስቃሴ ተገትቶ፣ አዲሱ ዘመቻ ፊቱን ወደ ጣሊያንና ኖርዌይ አዙሯል፡፡ ከዚያም ወደተለያዩ አገሮች ይቀጥላል፡፡
ባለፈው
ሳምንት የውኃ ሚኒስትሩ መሐመድ አብዱል ሙታሊብና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ነቢል ፋህሚ ወደ ጣሊያን ጉዞ
አድርገዋል፡፡ የግብፅ መንግሥት ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ ዋነኛ ሸሪክና የግድቡ ግንባታ...
Feb 26, 2014
የሱዳን ወዳጅነት ከጉርብትናም በላይ?
Geez Bet | Wednesday, February 26, 2014

ጠቅላይ
ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ በእያንዳንዱ የሕወሓት የልደት በዓል ማለትም የካቲት 11 በዋነኝነት ከሚከበርበት የትግራይ
ርዕሰ ከተማ መቐለ ተገኝተው በሚያደርጉት ንግግር በዓሉን ሁሌም ድምቀት ይሰጡት ነበር፡፡
ሥልጣን ላይ ያለው ኢሕአዴግ ዋነኛ መሥራች የሆነውን ሕወሓት የረጅም ጊዜ ጠንካራ ሊቀመንበሩን ያጣው ባለፈው ዓመት በዓሉን ከማክበሩ ስድስት ወራት በፊት ነበር፡፡
አቶ
መለስ ለመጀመርያ ጊዜ ያልተገኙበት 38ኛው በዓል ግን እሳቸውን በመዘከር በሐዘን ድባብ ነበር ያለፈው፡፡
ተተኪያቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝም በወቅቱ በበዓሉ ላይ ቢገኙም፣ በአቶ መለስ መሪነት እዚህ
ደርሷል ያሉት ሥርዓት ከፍተኛውን መስዋዕትነት ከፍሎበታል ካሉት ከትግራይ ሕዝብ ጋር እጅና ጓንት በመሆን
እንደሚሠሩ፣ ‹‹የማፅናኛ›› ንግግር አድርገው ነበር የተመለሱት፡፡
ዘንድሮ
...
Feb 24, 2014
ዝምተኛው የአውሮፕላን ጠላፊ
Geez Bet | Monday, February 24, 2014

ቅዳሜ የካቲት 8 ቀን 2006 ዓ.ም. የኢትዮጵያ
አየር መንገድ የደንበኞች ቀንን በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ባከበረበት ወቅት፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ተወልደ ገብረ
ማርያም በመቶዎች ለሚቆጠሩ የአየር መንገዱ ደንበኞች አየር መንገዱ ስለደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዝርዝር ማብራሪያ
ሲሰጡ ነበር፡፡
የአገር ባህል ልብስ ለብሰው ፈገግታ ሳይለያቸው የአየር
መንገዱን ስኬት ሲያስረዱ ‹‹ዋካ ዋካ›› በሚለው በሻኪራ ተወዳጅ ዜማ ታጅበው ነበር፡፡ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ
ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪና የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት አብዱሰላም አቡበከር፣ ታዋቂ ባለሀብቶችና ዲፕሎማቶች
በተገኙበት በዚህ ደማቅ ሥነ ሥርዓት ላይ አቶ ተወልደ የአየር መንገዱን ስኬት በኩራት አስረድተዋል፡፡
በእርግጥም አየር መንገዱ ባለፉት አምስት ዓመታት በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ይገኛል፡፡...
Feb 23, 2014
የኢቴቪ ዋና ዳይሬክተር ታስረው እንዲቀርቡ ታዘዘ
Geez Bet | Sunday, February 23, 2014

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት እየታየ በሚገኘው 28 ተከሳሾች
ላይ ለቀረበ የአቃቤ ህግ የቪዲዮ ማስረጃ አስተርጓሚ እንዲመድብ የታዘዘው የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት፤
የፍ/ቤቱን ትዕዛዝ ተግባራዊ ባለማድረጉ ዋና ዳይሬክተሩ ፍ/ቤት ታስረው እንዲቀርቡ ታዘዘ፡፡ በእነ አማን
አሠፋ መዝገብ በሚገኙ የሽብር ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ የሰው ምስክሮችንና በሺዎች የሚቆጠሩ የሰነድ ማስረጃዎችን
ለፍ/ቤቱ አቅርቦ ያጠናቀቀ ሲሆን በአረብኛና በኦሮሚኛ ቋንቋዎች ለቀረቡት የቪድዮ ማስረጃዎች ኢሬቴድ አስተርጓሚ
እንዲመድብ ከፍ/ቤቱ የተላለፈውን ትዕዛዝ ተግባራዊ አላደረገም ተብሏል፡፡ በዚህም ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ብርሃኑ
ኪዳነማርያም ታስረው ፍ/ቤት እንዲቀርቡ ታዟል፡፡ ቀደም ሲል እነዚህን የሽብር ተጠርጣሪዎች አስመልክቶ
በኢትዮጵያ...
Feb 23, 2014
በተጠለፈው አውሮፕላን ውስጥ የነበረው ኢትዮጵያዊ እማኝነት
Geez Bet | Sunday, February 23, 2014

“የተሳፋሪው ፍላጎት የሆነ መሬት ላይ ማረፍ ብቻ ነበር”በሃዋሳ ከተማ በተለምዶ ኬሮ ሰፈር እየተባለ
በሚጠራው አካባቢ ተወልዶ ያደገው ወጣት ምህረቱ ገብሬ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በቀድሞው ሀዋሳ ኮምቦኒ
የመጀመርያ ደረጃ ት/ቤት ነው የተከታተለው። የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያና የመሰናዶ ትምህርቱንም በቅዱስ ዳንኤል
ኮምቦኒ የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ት/ቤት አጠናቋል። ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2001 ዓ.ም በሲቪል ምህንድስና
የመጀመሪያ ዲግሪውን ካገኘ በኋላም፤ እስከ 2004 ዓ.ም ድረስ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በመምህርነት አገልግሏል፡፡
በመቀጠልም ነጻ የትምህርት ዕድል በማግኘት፣ ወደ ጣሊያን አምርቶ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በመከታተል ላይ
ይገኛል፡፡...
Feb 20, 2014
መሬትና ዉሃ ቅርምት በኢትዮጵያ
Geez Bet | Thursday, February 20, 2014

ኢትዮጵያ ዉስጥ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቡን እየጎዳ እንደሚገኝ ዓለም ዓቀፉ የመብት ተሟጋች ሂዉማን ራይትስ
ዎች አመለከተ። ድርጅቱ ይህን አመልክቶ ባወጣዉ ዘገባ በዚህ ምክንያትም ኢትዮጵያና ኬንያ ዉስጥ 500,000 አርብቶ
አደሮች ለችግር መጋለጣቸዉን ገልጿል።
ሂዉማን ራይትስ ዎች፤ ኢትዮጵያ፤ የመሬትና ዉሃ ቅርምት ማኅበረሰቦችን ጎዳ በሚል ዛሬ ባወጣዉ ዘገባ፤
አዳዲስ ከሳተላይት የተገኙ ምስሎች በታችኛዉ ኦሞ ሸለቆ አካባቢ ነባር ማኅበረሰቦች ይጠቀሙበት የነበረዉን መሬት
ለስኳር ልማት በስፋት መመንጠሩን ማሳየታቸዉን አመልክቷል። ላለፉት አምስት ወራትም 7,000 የሚሆኑ የቦዲ ጎሳ
አባላት ጋ በቂ ምክክር ሳይደረግ ተግባሩ መከናወኑን ዘርዝሯል። የድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳይ ምክትል ዳይሬክተር ሌስሊ
ሌፍኮ፤ ድርጅታቸዉ በUNESCO በዓለም ቅርስነት...
Feb 19, 2014
Sudan FM criticises Egypt over Ethiopian dam dispute
Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014

February 18, 2014 (KHARTOUM) –Sudanese foreign minister Ali Karti has
criticised Egypt for its handling of a dispute involving the
construction of a massive dam project in Ethiopia, which it has
vehemently opposed over concerns it could disrupt water flows from the
Nile river.
Karti said Egypt was further inflaming the situation by making
critical comments in the media, adding that Sudan would continue its
efforts to bridge the gap between the two countries.
“The position
of Sudan...
Feb 19, 2014
የጠላፊው ረዳት አብራሪ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል
Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014

- መንግሥት ተላልፎ እንዲሰጠው ይፈልጋል:
ባለፈው
እሑድ ሌሊት 6፡30 ሰዓት ከአዲስ አበባ ወደ ሮም መብረር የጀመረውን የበረራ ቁጥሩ ‹‹ET 702›› የኢትዮጵያ
አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን የጠለፈው ረዳት አብራሪው ኃይለመድኅን አበራ ተገኝ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
ጠለፋውን ፈጸመ የተባለው ረዳት አብራሪ ቤተሰቦች መሆናቸውን የሚናገሩ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኃይለመድኅን ላይ ያልተለመዱ ባህሪዎችን መመልከታቸውን ይናገራሉ፡፡
ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ደግሞ ግለሰቡ በተለያዩ ጊዜያት የዲስፒሊን ችግሮች ቢኖሩበትም፣ ብቃት ያለው አብራሪ እንደነበረ ገልጸዋል፡፡
ጉዳዩን
በተመለከተ ባለፈው ሰኞ ከቀትር በኋላ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚነስትር
አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ግለሰቡ ጠለፋውን ለመፈጸም ምን...
Feb 19, 2014
ሦስት የግብፅ የፖለቲካ ፓርቲዎች ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲቋረጥ ለዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረቡ
Geez Bet | Wednesday, February 19, 2014

የታላቁ
የህዳሴ ግድብ ግንባታን በተመለከተ ሲካሄድ የቆየው የሦስትዮሽ ውይይት ከተቋረጠ ከሳምንታት በኋላ፣ ሰሞኑን ሦስት
የግብፅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የግድቡ ግንባታ እንዲቋረጥ ለዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረቡ፡፡
‘ዲሞክራቲክ
ፒፕል ፓርቲ’፣ ‘ኢጂፕቲያን ዓረብ ሶሻሊስት ፓርቲ’ እና ‘ሶሻል ጀስቲስ ፓርቲ’ የተባሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች
በጋራ ዘ ሄግ ለሚገኘው ዓለም አቀፍ የፍትሕ ፍርድ ቤት፣ ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ እንድታቆም የሚጠይቅ ማመልከቻ
አስገብተዋል፡፡
ግብፅ
በየዓመቱ 55 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውኃ ከዓባይ ተፋሰስ እንደምትጠብቅ የተናገሩት የዲሞክራቲክ ፒፕል ፓርቲ
ሊቀመንበር ፉአድ ሃፌዝ፣ ባለፈው መስከረም ወር የወንዙ ፍሰት በ20 ቢሊዮን ኪዩቡክ ሜትር ቅናሽ ማሳየቱን
አመልክተዋል፡፡
የፍርድ
ቤቱን አንቀጽ 40 እና የተባበሩት...
Feb 17, 2014
Co-pilot hijacks plane to Geneva, seeks asylum
Geez Bet | Monday, February 17, 2014

GENEVA (AP)
-- An Ethiopian Airlines co-pilot locked his colleague out of the
cockpit, hijacked a Rome-bound plane and landed Monday in Geneva, all in
an attempt to seek asylum in Switzerland, officials said.
The
Boeing 767-300 plane with 202 passengers and crew had taken off from
the Ethiopian capital of Addis Ababa and landed in the Swiss city at
about 6 a.m. (0500 GMT). Officials said no one on the flight was injured
and the hijacker was taken into custody after surrendering...
Feb 17, 2014
አሳሳቢው የመምህራን ፍልሰት
Geez Bet | Monday, February 17, 2014

ቦሌ መሰናዶ ትምህርት ቤት ውስጥ መምህራንና ተማሪዎች በመማር ማስተማሩ ሒደት ለመምከር ተሰባስበዋል፡፡
የ‹‹ትምህርት ለሁሉም›› 2013/14 ሪፖርት ይፋ
መሆንን ተከትሉ ውይይቱን ለማድረግ ለተወከሉት ተማሪዎች ሴራሊዮናዊው አወያይ ቼርኖር ባህ ‹‹መምህር መሆን የሚፈልግ
አለ?›› ሲል ጥያቄውን ሰነዘረ››፡፡ ከደቂቃዎች ዝምታ በኋላ አንድ ተማሪ ‹‹እኔ መሆን እፈልጋለሁ፡፡ አንድ
ጥያቄ ለመምህራኑ እንድጠይቅ ግን ፍቀድልኝ›› አለች፡፡ ሚስተር ባህ መድረኩን ሰጣት፡፡ ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣
ከማላዊና ከፓኪስታን ለተወከሉት መምህራን ‹‹ከእናንተ ውስጥ ልጁ መምህር እንዲሆን የሚፈልግ አለ?›› ስትል
ጠየቀች፡፡ አንድም መምህር አዎ ሲል አልተደመጠም፡፡
ቤተሰብ በልጁ ላይ ከሚፈጥረው የ‹‹መምህር አትሆንም›› ተፅዕኖ በተቃራኒ ልጁ መምህር እንዲሆንለት...
Feb 17, 2014
‹‹ከኢትዮጵያ ጋር ከመደራደር ይልቅ ሌሎች አማራጮችን መውሰድ እንፈልጋለን›› የግብፅ የውኃ ሚኒስትር
Geez Bet | Monday, February 17, 2014

-ግብፅ ከኢትዮጵያ ጀርባ ቱርክ አለች ማለት ጀመረች
ባለፈው ሰኞ በአዲስ አበባ ለውይይት መጥተው ስብሰባው
ተቋርጦ ወደ አገራቸው የተመለሱት የግብፅ የውኃና መስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ካይሮ ሲደርሱ በሰጡት
መግለጫ፣ ከኢትዮጵያ ጋር መደራደር እንደበቃቸው ከገለጹ በኋላ ‹‹ሌሎች አማራጮችን መውሰድ እንፈልጋለን፤››
ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ በደፈናው ሌሎች አማራጮችን ከማለት ውጪ
ማብራሪያ አልሰጡም፡፡ ይሁን እንጂ ንግግራቸውን በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ያነበቡ ኢትዮጵያውያን ንግግሩን ፀብ
አጫሪነት ነው ብለው፣ ‹‹ኢትዮጵያውያን ግድቡን እንገነባለን፣ ግብፆች ያላቸው ሌላ አማራጭ ምን እንደሆነ
እናያለን፤›› በማለት በቁጣ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
‹‹የኢትዮጵያ የመንግሥት ባለሥልጣናት ግብፅን የመጉዳት ፍላጎት የለንም እያሉ ነው፡፡...
Feb 15, 2014
የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ሠራተኞች በአስተዳደራዊ ችግር ተማረናል አሉ
Geez Bet | Saturday, February 15, 2014

“የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች አሉባልታ ነው” - ዩኒቨርስቲውበባህርዳር ዩኒቨርስቲ አስተዳደራዊ
ችግር መማረራቸውን የተናገሩት የዩኒቨርስቲው ሠራተኞች፤በየጊዜው መምህራን ሥራቸውን እየለቀቁ እንደሚወጡ ገለፁ፡፡
የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ባይሌ ዳምጤ በበኩላቸው፤ የግንዛቤ ችግር ያለባቸው ሰራተኞች አሉባልታ እንጂ
በዩኒቨርስቲው ውስጥ አስተዳደራዊ ችግር እንደሌለ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ በዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ብር
በላይ በጀት የሚመደብለት፣ ከ45 ሺህ በላይ ተማሪዎች የሚያስተምርና ከአምስት ሺህ በላይ ሰራተኞች የሚያስተዳድረው
ዩኒቨርስቲው፤ ከአመራርና አስተዳደር ሙያ ጋር የተገናኘ የትምህርት ዝግጅት በሌላቸው አመራሮች እየተመራ፣ ለከፍተኛ
አስተዳደራዊ ችግር መጋለጡን ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልፀዋል፡፡ አንድ የዩኒቨርስቲው ሠራተኛ በሰጠው...
Feb 13, 2014
‹‹ከኢትዮጵያ ጋር መታረቅ ስለሚባለው ባልሰማውና ባላስበው እመርጣለሁ›› ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ
Geez Bet | Thursday, February 13, 2014

የቀድሞው
የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የሥልጣን ዘመናቸውን ከጨረሱ በኋላ፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ
መንግሥታትን ማስታረቅ እንደሚፈልጉ የመንግሥት የቴሌቪዥን ጣቢያ በሆነው ኢቴቪ በይፋ ገልጸው መስመር የያዘላቸው
መሆኑንም አሳውቀው ነበር፡፡
በቅርቡ
ከኤርትራ ቴሌቪዥን ጋር ሰፊ ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግን ምንም ዓይነት የዕርቅ ፍላጐት
እንደሌላቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በፕሮፓጋንዳ ብልጫ እየተጠቀመበት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያን
በተመለከተ ለቀረቡላቸው ጥያቄ የሰጧቸው ምላሾች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡
‹‹የሕዝብ ግንኙነት ብልጫ ለማግኘት ነው››
ሁለት
የኤርትራ የመንግሥት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች አንዳንድ የአገር ውስጥና የአካባቢ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ ጥያቄዎችን
ለፕሬዚዳንት ኢሳያስ...
Feb 13, 2014
የግብፅ ሚኒስትር የግድቡ ግንባታ እንዲቆም በመጠየቃቸው ውይይቱ ተቋረጠ
Geez Bet | Thursday, February 13, 2014

የግብፅ
የውኃና መስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ በጠየቁት
መሠረት ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ ቢገቡም፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እንዲቆም በመጠየቃቸው ውይይቱ በሰዓታት
ውስጥ ተቋረጠ፡፡
የግብፅ ሚኒስትር ከኢትዮጵያ አቻቸው አቶ አለማየሁ ተገኑና ከባልደረቦቻቸው፣ እንዲሁም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተወከሉ ባለሙያዎች ጋር ባለፈው ሰኞ መገናኘታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በታላቁ
የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና ተያያዥ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ከጋዜጠኞች
ጋር ለመወያየት ባዘጋጀው መድረክ ላይ የተገኙት አቶ አለማየሁ ተገኑ፣ የግብፅ አቻቸው ሁለት አጀንዳዎችን ይዘው
መቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡
የግብፅ
ሚኒስትር በስልክ ደውለው ወደ አ...
Feb 10, 2014
የአንድነት ፓርቲ አመራር አቶ አሥራት ጣሴ ታሰሩ
Geez Bet | Monday, February 10, 2014

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የምክር ቤት አባል አቶ አሥራት ጣሴ ፍርድ ቤት በመድፈር ወንጀል ተከሰው ጥፋተኛ በመባላቸው፣ ጥር 30 ቀን 2006 ዓ.ም. በፖሊስ ጣቢያ ታሰሩ፡፡
አቶ አሥራት ለእስር የበቁበትን ፍርድ ቤት የመድፈር ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት፣ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ቅጽ 7 ቁጥር 198 የጥር ወር 2006 ዓ.ም. ዕትም ላይ በጻፉት ጽሑፍ ምክንያት ነው፡፡
አቶ አሥራት በመጽሔቱ ላይ ባሰፈሩት ‹‹…..አሁን ደግሞ ከሰሞኑ ‘አኬልዳማ’ ድራማ በድጋሚ በተከታታይ
እየቀረበ ነው፡፡ ይህ እየሆነ ያለው አንድነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅትን በስም ማጥፋት ወንጀል በፍርድ
ቤት ከሶ ገና ውጤት ባልተገኘ...
Feb 10, 2014
የግብፅ እጅ መንሻ?
Geez Bet | Monday, February 10, 2014

በተጠናቀቀው ሳምንት የግብፅ ወጣት የዲፕሎማሲ
ሠልጣኞች ቡድን በአዲስ አበባ የአንድ ሳምንት ቆይታ አድርጓል፡፡ ሪፖርተርን ጨምሮ የተወሰነ ቁጥር ያላቸው
ጋዜጠኞችም ጥሪ ተደርጐላቸው ከግብፅ ልዑካን ቡድን ጋር ለመነጋገርና ለመወያየት ተጋብዘዋል፡፡
በኢትዮጵያ የግብፅ አምባሳደር መሐመድ እድሪስ ስለ ቡድኑ
መምጣት፣ ዓላማና ግብ እንዲሁም የቡድኑ አባላት ማንን እንዳነጋገሩ፣ የት የት እንደሄዱ ገልጸው፣ በየዓመቱ የግብፅ
መንግሥት ሠልጣኝ ዲፕሎማቶቹን ወደ ኢትዮጵያና ሌሎች አፍሪካ አገሮች ልምድ እንዲቀስሙ እንዲህ ዓይነት ጉዞ
እንደሚያዘጋጅላቸውና ይህም እጅግ ጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዲፕሎማሲያዊ ጉዞው ብቻ እንደ አንድ ልማድ ተደርጐ
እየተወሰደ መሆኑን በኤምባሲው ለተገኙ የአገር ውስጥ ጋዜጠኞች ገለጻ አድርገዋል፡፡
የግብፅ አምባሳደር መሐመድ እድሪስ፣...
Feb 5, 2014
ጉራማይሌ ፖለቲካ! (ተመስገን ደሳለኝ)
Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014

በምንወዳት ኢትዮጵያችን ከኑሮ እስከ ሮሮ፤ ከማሕበራዊ እስከ ፖለቲካ፤ ከኢኮኖሚ እስከ ትምህርት ፖሊሲ፤ ከመንፈሳዊ እስከ ዓለማዊ… ያሉ ጉዳዮች ጉራማይሌነት ከቀን ወደ ቀን እየጎላ ነው፡፡ በዚህ ፅሁፍም ጥቂት ያህል ማሳያዎችን በአዲስ መስመር እንመለከታለን፡፡ጎንደር እና ጥምቀትየሁሉም መነሻና መድረሻ ዓላማ መንፈሳዊ ይሁን እንጂ እንደ መስቀል፣ ጥምቀትና ሬቻ… ያሉ አንዳንድ በዓላት ከመንፈሳዊነታቸው በተጨማሪ የባሕል መገለጫ እስከመሆን ደርሰዋል፡፡ ከዚህ የተነሳም በዓላቶቹ በሚከበሩባቸው ቦታዎች የሚገኘው ስፍር ቁጥር የሌለው ሕዝብ፣ ሰማያዊውን ፅድቅ ብቻ ሳይሆን፣ በባህላዊው አከባበርም በእጅጉ ስለሚማርክ ጭምር ነው፡፡የሆነው ሆኖ በወዳጆቼ ጋባዥነት የዛሬ አስራ አምስት ቀን በጎንደር ከተማ በተከበረው የጥምቀት በዓል ላይ ተገኝቼ ነበር፤ በወቅቱም የታዘብኩት ጉዳይ ከሺህ ዓመታት በፊት...
Feb 5, 2014
ግብፅ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ጀመረች
Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014

-የግብፅ የልዑካን ቡድን በህዳሴው ግድብ ላይ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር ሊነጋገር ነው
የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በተመለከተ ሱዳን ለኢትዮጵያ የሰጠችውን ድጋፍ ለማጨናገፍ፣ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ መጀመርዋን ዘገባዎች አመለከቱ፡፡
የተለያዩ የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ሰሞኑን እንደዘገቡት፣ የግብፅ መንግሥት የተለያዩ የመንግሥት አመራሮችና ፖለቲከኞች ከሱዳን መንግሥት አቻዎቻቸው ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጀምረዋል፡፡
ለአብነት ከተጠቀሱት መካከል የግብፅ አል ዋፍድ ፓርቲ ሊቀመንበር ሳይድ አል ባዳዊ በካይሮ ከሱዳን አምባሳደር
ከማል ሐሰን ዓሊ ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበር የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በዋነኝነት መክረዋል፡፡ በሁለቱ አገሮች ድንበር
የጦር መሣሪያ ዝውውር ለማስቆም የተነጋገሩት ሁለቱ ባለሥልጣናት፣ ኢትዮ...
Feb 5, 2014
የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ተማሪዎች ተጋጩ
Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014

በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ የኢንቫይሮመንታል ኢንጂነሪንግ
ተማሪዎች ‹‹ኢንቫይሮመንትን በሚመለከት የምንማረው ትምህርት ስለሌለ ካሪኩለሙ ተቀይሮ ኃይድሮሊክ ኢንጂነሪንግ
በሚል ይቀየርልን›› በማለት ከጥር 23 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮችና የፖሊስ ሠራዊት ጋር
መጋጨታቸውን፣ በሥፍራው የተገኙ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡
ዩኒቨርሲቲው ፈንድ ስለሚያገኝበት ብቻ ኢንቫይሮንመንታል
ኢንጂነሪንግ በሚል ስያሜ የማይማሩትን ትምህርት እንደተማሩ በማስመሰል ዲግሪ የሚሰጣቸው ከሆነ፣ በማይታወቅና ምንም
ጥቅም በሌለው የትምህርት መስክ ከመቀመጥ ባለፈ ሌላ ጥቅም እንደማያገኙበት በመግለጽ፣ ካሪኩለሙ እንዲቀየር አጥብቀው
መጠየቃቸውን ሪፖርተር ያጋገራቸው አንዳንድ ተማሪዎች አስረድተዋል፡፡&nbs...
Feb 5, 2014
የእግር ኳሱን አንኳር ችግር መንካት የተሳነው ግምገማ
Geez Bet | Wednesday, February 05, 2014

ክስተቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በጥሩም በመጥፎም እያነጋገረ ሰንብቷል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት አንዳንዶች ‹‹በአጋጣሚ›› አንዳንዶች ደግሞ ‹‹በጥረት›› በሚሉት መንገድ ወደ አፍሪካ ዋንጫ፣
እንዲያም ሲል ለዓለም ዋንጫ ማጣርያ ከአሥር የአፍሪካ ምርጦች አንዱ ሆኖ የመጣው የዋሊያዎቹ ቡድን፣ እንደ አመጣጡ መጓዝ ተስኖት የተሰናበተ የቻን የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ትዝብት ውስጥ ጥሎታል፡፡
አንድም ጐል ሳያስቆጥር በሁሉም ግጥሚያዎች ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ መሆኑ ብዙ አስነቅፎታል፡፡ ከሕዝቡ
የተሰነዘረበት ትችት የበረታ መሆኑን ተከትሎ ተጨዋቾቹ፣ አሰልጣኙና ሌሎችም በቡድኑ ውስጥ ኃላፊነት ያላቸው አካላት
ቅሬታቸውን ሲያ...
Feb 4, 2014
የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ከአገር ኮበለሉ
Geez Bet | Tuesday, February 04, 2014

የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩትና በአሁኑ ሰዓት የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት የተከበሩ
አቶ ኡመድ ኡባንግ፤ ከአገር መኮብለላቸውን ምንጮቻችን ገለፁ፡፡ አቶ ኡመድ ኡባንግ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ
ከሃገር መውጣታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለሱ ለሚቀርቧቸው ሰዎች መናገራቸውን አመልክተዋል።
የሚኒስትር ዴኤታውን መኮብለል በተመለከተ የጠየቅናቸው የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም፤ አቶ
ኡመድ በስራ ገበታቸው ላይ እንደሌሉ ማረጋገጣቸ...