Time in Ethiopia:

Sep 23, 2013

አፍሪካና የማያባራው እልቂት

Geez Bet | Monday, September 23, 2013
የውጭ ሀገር ዜጎች ጥላቻ ዳግም በደቡብ አፍሪቃ መቀስቀሱ፣ በፍፁማዊ የዘውድ አገዛዝ በምትመራው አነስተኛዋ የአፍሪቃ ሀገር የምርጫ ሂደት፣ እንዲሁም ሶማሊያን የሚመለከት ጉባኤ በብራስልስ የተሰኙት ርዕሰ ጉዳዮች በትኩረት በአፍሪቃ ዝግጅታችን ከተካተቱት ጥንቅሮች ዋነኖቹ ናቸው።
ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ፖርት ኤሊዛቤዝ በተሰኘው አካባቢ የውጭ ሀገር ጥላቻ የተጠናወታቸው ግለሰቦች ሰሞኑን የሶማሊያውያን የሆኑ ንብረቶችን ሲመዘብሩ፣ ሲዘርፉ ብሎም እሳት ሲለቁባቸው ቆይተዋል። ከ1200 የሚበልጡ ሶማሊያውያንም ለህይወታቸው በመስጋት ቤት ንብረታቸውን ጣጥለው በሽሽት ላይ ይገኛሉ። አብዛኞቹም ታሪክ እራሱን እንዳይደግም አጥብቀው ሰግተዋል። የዛሬ አምስት ዓመታት ግድም
ሙሉውን አንብብ-Read More

Sep 18, 2013

መርዘኛ የጋዝ ጦር መሣሪያዎች

Geez Bet | Wednesday, September 18, 2013
ሰዎች ካለፈ እጅግ መጥፎ ድርጊት ፣ እስከምን ድረስ ትምህርት ይቀስማሉ? በተለያዩ ዘመናት ያጋጠሙ ሁኔታዎችን ፤ ጦርነቶችን ፤ ወረራዎችን ፤ ውዝግቦችን ስንመረምር ፣ ሰው፤ ጭካኔ የሚያሳይባቸው መሣሪያዎች በሥነ ቴክኑኒክ ተሻሽለው ተሠርተው ከመቅረባቸው 
በስተቀር፤ እርሱ ራሱ የባህርይ ለውጥ ያሳየበት ሁኔታ የለም። በቅዱሱ መጽሐፍ እንደተገለጠው ፤ ቃየል ብቸኛ ታናሽ ወንድሙን፤ አቤልን በድንጋይ ቀጥቅጦ ነው የገደለው። የዛሬው ዘመን ሰው «ወንድሙ» ን ፣ በአብራሪ- የለሽ አኤሮፕላን፣ ወይም በሚሳይል ወይም በመርዘኛ ጋዝ ማጥፋት ይችላል።
ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኀን፤ ሰሞኑን በተደጋጋሚ ካነሱአቸው ጉዳዮች አንዱ በሶሪያ ፣ ረቡዕ ፤ ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ ም፤
ሙሉውን አንብብ-Read More

Sep 4, 2013

የሶሪያ ጦርነትና የኃያሉ ዓለም ዝግጅት

Geez Bet | Wednesday, September 04, 2013

ፕሬዝዳት ኦባማ የሚተማመኑበትን እቅዳቸዉ ለማስፈፀም-የሚተማመኑበትን ዘመናይ ጦር ከምርጥ መሳሪያዎቹ ጋር አዝምተዋል።የሶሪያ የቅርብ ወዳጆች ሩሲያ፥ ቻይና እና ኢራን የድብደባዉን ዕቅድና ዘመቻ አጥብቀዉ ይቃወማሉ።የሩሲያዉ ፕሬዝዳት ቭላድሚር ፑቲን ከዚሕም አልፈዉ አሜሪካና የተባባሪዎችዋን አቅድ አጣጥለዉ ነቅፈዉታል።
ሶሪያዎች ሠወስት ዓመት እንደለመዱት ይተለላለቃሉ።ለንደኖች፥ የደማስቆ መንግሥትን በኬሚካዊ ጦር መሳሪያ ሕዝብን በመጨረስ ወነጀሉ፥ ሶሪያን ለመብደብ ዛቱ፥ ፎከሩና በስተመጨረሻዉ ገሸሽ-ገለል አሉ።ፓሪሶች እንደ ለንደን፥ ዋሽግተኖች ዛቱ ፎከሩና የድብደባ-ነጋሪቱ ዋሽንግተን ላይ እስኪጎሰም አድፈጠዉ ቀሩ።ዋሽግተኖች እንደፎከሩ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Aug 19, 2013

በግብጽ አስከሬን፣ ቤቴክርስቲናያት እና መስጊድ በእሳት እየተቃጠሉ ነው!

Geez Bet | Monday, August 19, 2013
   
ግብፅ ጥይት፥ አረር፥ እየዘራች፥ አስከሬን-አጭዳ በእሳት ታጋያለች።ያቺ አስከሬን ለዝንታ-ዓለም የሚቀመጥባት ሐገር ዛሬ የሰዉ አካል ይተለተልባታል።ያቺ የጥንታዊ ሥልጣኔ ጎተራ፥ ያቺ የታሪካዊ የቅርስ ቋት፥ ያቺ ሥልታዊት ሐገር ታወረች? ወይስ አበደች? እዉሩ ወይም እብዱስ ማነዉ?
የግብፅ ጦር ዘመን ባፈራዉ ዘመናይ ጦር መሳሪያ መግደል፣ መደብደብ ማሰሩን፣ ሙስሊም ወንድማማቾች እምነት፣ቁጭት ና እልሕ በወለደዉ ፅናት መፋለሙን እንደቀጠሉ ነዉ።የዘመኑ ፈርዖኖች ፍሊሚያ የፈረዕኖቹን ዉልድ እየፈጀ፣ የፈርዖኖቹን ታሪካዊ፣ ሥልታዊት ሐገርን እያወደመ-ቁል ቁል ያንደረድራታል።የጥፋት ዉድመቱ ሒደት፣ ዉጤት መዘዝ አረብ አይሁድን፣ አፍሪቃ እስያን፣ ከሁሉም በላይ አዉሮጳ አሜሪካን እያሳሰበ ግን አቋማቸዉን እያዋዠቀ ነዉ።የግብፅ እልቂት-ዉድመት መነሻ የሁለቱ ፈርዖኖች ደምሳሳ ቅኝት ማጣቀሻ፣ የተቀረዉ ዓለም አቋም መድረሻችን ነዉ ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።
ሙሉውን አንብብ-Read More

Aug 12, 2013

በአዲስ አበባ ግብረሰዶም በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ነው!

Geez Bet | Monday, August 12, 2013
 Addis Admass 
*ግብረሰዶማዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ “ሬንቦ” የተባለ ማህበር አቋቁመዋል
*በግብረሰዶማውያን ዙርያ የተካሄዱ ጥናቶች አዳዲስ መረጃዎችን ይፋ አድርገዋል
*ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናትና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የጥቃት ሰለባ ሆነዋል
*ኢትዮጵያውያን ከተመሳሳይ ፆታ ጋር ወሲብ ሲፈፅሙ የሚያሳዩ ፊልሞች ለገበያ ቀርበዋል
            ከወራት በፊት እዚህ አዲስ አበባ ከተማችን ውስጥ የተፈፀመ ታሪክ ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመው በአንድ ስመ-ጥር የወንዶች ልብስ መሸጫ ቡቲክ ውስጥ ነው፡፡ ወጣቱ በቡቲኩ ውስጥ ተቀጥሮ መስራት ከጀመረ ቆየት ብሏል፡፡ በአለባበሱ ሽቅርቅርና ዘመናዊ ነው፡፡ ወደ ቡቲኩ የሚመጡትን ደንበኞች በፈገግታና በትህትና እየተቀበለ ያስተናግዳል፡፡ ደንበኞች የፈለጉትን ልብስ አስወርደው ለመለካት ወደ መልበሻ ክፍል ሲገቡ በዓይኑ ይከተላቸዋል፡፡ በገቡበት የመልበሻ ክፍል መጋረጃ ላይ አይኖቹን
ተክሎ ለደቂቃዎች እንደሚቆይ የቡቲኩ ባለቤት ብዙ ጊዜ ታዝቦታል፡፡ ሆኖም ደንበኞቹ አዲሱን ልብስ ለብሰው ሲወጡ ለማየት ከመጓጓት የተነሳ እየመሰለው በዝምታ ያልፈዋል፡፡ “ለምን እንዲህ ታያለህ?” ብሎ ጠይቆት አያውቅም
ሙሉውን አንብብ-Read More

Aug 6, 2013

“ሹገር ማሚዎች” የከተማችንን ጎረምሶች እያጠመዱ ነው

Geez Bet | Tuesday, August 06, 2013
መታሰቢያ ካሣዬ 
 
የሴትየዋ የፊት ገፅታ የዕድሜያቸውን መግፋት ቢያጋልጥም በተለያዩ ሜካፖችና ቅባቶች እንዲሁም በዘመናዊ አለባበሣቸው ወጣት ለመምሰል ጥረዋል። እንዲህ ያሉ ወይዘሮዎች በአብዛኛው አንቱ መባልን አጥብቀው እንደሚጠሉ ያውቃል። ለዚህም ነው “አንቺ” እያለ ማናገር የጀመረው። አዲሷ የጂም ተማሪ፣ ወጣቱ ላይ ዓይናቸውን ጥለዋል፡፡ ዘንካታነቱና የስፖርተኛ ቁመናው ማርኳቸዋል፡፡
   የተስተካከለ ቁመናውና የስፖርተኛ አቋሙ የብዙ ሴቶችን ዓይን ይስባል፡፡ ጐተራ አካባቢ በሚገኝ አንድ ጂምናዚየም ውስጥ ተቀጥሮ ደንበኞቹን ስፖርት ያሰራል፡፡ በተግባቢነቱ፣ በተጨዋችነቱና በሰው አክባሪነቱ ሁሉም ይወዱታል፡፡ ከሥራው ቦታ ሳይርቅ ጎተራ ላንቻ አካባቢ ከግለሰብ በተከራየው አንድ ክፍል ቤት ውስጥ እየኖረ ሳለ ነው ህይወቱን የሚቀይር አንድ አጋጣሚ የተፈጠረው፡፡ ያቺን ዕለት አይረሳትም፡፡ ሴትየዋ ጠና ያሉ ናቸው - ከ50 ዓመት በላይ ይሆናቸዋል፡፡ የተደላደለ ኑሮ እንዳላቸው ሁለመናቸው ይናገራል፡፡ የጂም ደንበኛ ሆነው ሲመዘገቡ ምንም የተለየ ነገር ይፈጠራል ብሎ አላሰበም፡፡ እንደ ሁልጊዜው በፈገግታና በትህትና ተቀብሎ አስተናገዳቸው፡፡
የለበሰው ቲ-ሸርትና ቁምጣ በጡንቻዎቹ ተወጣጥሯል፡፡ አይናቸውን ከሱ ላይ መንቀል ተሣናቸው፡፡ በስፖርት ሰበብ መቀራረብና መነካካት መኖሩን ደግሞ ወደውታል፡፡ ከወገብሽ ጎንበስ እግርሽን ከፍ ክንድሽን ዘርጋ ከደረትሽ ገፋ እያለ ---የሚሰሩትን እንቅስቃሴ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jul 31, 2013

በዓባይ ጉዳይ የግብፅ መንግሥት ሠራዊቱን በተጠንቀቅ እንዲቆም አዘዘ

Geez Bet | Wednesday, July 31, 2013
By: Ethiopian Reporter
 ሱዳን በቅርቡ ከግብፅ ጐራ ልታፈነግጥ ትችላለች
በዘካሪያስ ስንታየሁ
አዲሱ የግብፅ መንግሥት በዓባይ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ሊነሳ በሚችል ግጭት ምክንያት ሠራዊቱን በተጠንቀቅ እንዲቆም ቢያዝም፣ የግብፅ የጦርነት እንቅስቃሴ ትኩረት ለማስቀየር መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ፡፡
ኢትዮጵያ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሱዳን ጠረፍ 40 ኪሎ ሜትር ወደ ውስጥ ገባ ብላ በምትገኘውና ቡምባዲ በምትባለው አካባቢ 5,250 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለውን ታላቁ የሚሌኒየም ግድብ ፕሮጀክት ይፋ ካደረገች በኋላ፣ ግብፅ የተለያዩ ጫናዎችን በኢትዮጵያ ላይ ለማሳደር እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች፡፡ ግብፅም በዚህ ግድብ ምክንያት የዓባይ የውኃ መጠን ሊቀንስ ይችላል የሚል ስጋት ስላላት፣ የዲፕሎማሲ ጫና ከማድረጓ በተጨማሪ የጦር ሠራዊቷን በተጠንቀቅ እንዲቆም እስከማዘዝ ደርሳለች፡፡
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jul 27, 2013

የነጀማነሽ ማህበር ከነብዩ ኤልያስ ለፓትርያርኩ አመጣን ያሉትን መልእክት ይፋ አደረጉ

Geez Bet | Saturday, July 27, 2013
አርቲስት ጀማነሽ ሰሎሞንን ያካተተው የማህበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አባላት፣ ለፓትርያርኩ ያመጣነውን “የቅዱስ ኤልያስ” መልእክት የሚቀበለን አጥተናል በማለት ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ አደረጉ፡፡ በብሔረ ሕያዋን ይኖራል ከተባለው ነብዩ ኤልያስ ተልከን መልእክታችንን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ እንዳናደርስ የጥበቃ አባላት ከልክለውናል ያሉት የማህበሩ አባላት፤ ከመልዕክቶቹ መካከል ትክክለኛው ሰንበት ቅዳሜ ስለሆነ በእሁድ ፋንታ በብሔራዊ ደረጃ ታውጆ መከበር ይገባዋል የሚል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ “ኦርቶዶክስ” የሚለውን ስያሜ የሚቃወሙት የማህበሩ አባላት፤ “ተዋህዶ” የተሰኘው እምነት ጥንታዊ የጉባኤ እለታትን ጨምሮ አራት የቅዱሳን መታሰቢያ ቀናት በብሔራዊ በዓልነት ለማስከበር ፓትሪያርኩ ከፌደራል መንግስቱ ጋር መነጋገር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡
ሙሉውን አንብብ-Read More

ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማሪያም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ግልፅ ደብዳቤ ላኩ

Geez Bet | Saturday, July 27, 2013
የቤኒሻንጉል ተፈናቃዮች አሁንም በችግር ላይ ናቸው” (መኢአድና ሠማያዊ ፓርቲ)
ከቤኒሻንጉል ክልል ተፈናቅለው ከነበሩት የአማራ ክልል ተወላጆች ጋር በተያያዘ የክልሉን የስራ ሃላፊዎችና መንግስትን ለመክሰስ፣ ሰማያዊ ፓርቲና መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ጥብቅና ያቆሟቸው አለም አቀፍ የህግ ባለሙያው ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማሪያም፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ግልፅ ደብዳቤ መፃፋቸው ተገለፀ፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች ከትናንት በስቲያ ከሠዓት በኋላ በሠማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጋራ በሠጡት መግለጫ፤ ተፈናቃዮቹ አሁንም ችግር ላይ መሆናቸውን፣ ልጆቻቸው ትምህርት ማቋረጣቸውን፤ በሚዲያ እንደሚነገረው ወደ ቀድሞ ኑሯቸው አለመመለሳቸውንና በአጠቃላይ ችግር ላይ መሆናቸውን
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jul 24, 2013

አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ ፕሬዚዳንት ለመሆን ጓጉቷል

Geez Bet | Wednesday, July 24, 2013
ወደ ፖለቲካ የምገባው ህዝብ ማገልገል ስለምፈልግ ነው
*
ኢትዮጵያን አርቀንና በረጅም ጊዜ የማናይ ከሆነ፣አባይን መገደብ አያስፈልገንም
*
በውጭ ሆነው የሚቃወሙ አገራቸው ላይ መታገል አለባቸው ባይ ነኝ

ከጥቂት ዓመታት በፊት /ሚኒስትር የመሆን ፍላጐት እንዳለው ገልፆ የነበረው አትሌት ኃይሌ /ሥላሴ፤ ሰሞኑን ከአሶሼትድ ፕሬስ ጋር ባደረገው ቃለምልለስየአገሪቱ ፕሬዚዳንት መሆን እፈልጋለሁበማለቱ የመነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኗል፡፡ 2007 . በሚደረገው አገራዊ ምርጫ ተወዳድሮ ፓርላማ ለመግባት ያሰበው አትሌቱ፤
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jul 15, 2013

አምባሳደር ዘውዴ ረታ

Geez Bet | Monday, July 15, 2013

‹‹በስሚ ስሚ ከየትም የሚለቃቀሙ ታሪኮች ናቸው ችግር እየፈጠሩ ያሉት››

አምባሳደር ዘውዴ ረታ በቀዳሚዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በጋዜጠኝነትና በዲፕሎማትነት ሲታወቁ በዚህ ዘመን ደግሞ የታሪክ ተመራማሪና ጸሐፊ ናቸው፡፡
ታሪክ ሲጽፉም ማስረጃዎችን በሚገባ እንደሚያገላብጡና እንደሚመረምሩ ይነገርላቸዋል፡፡ በተለይ ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ ለንባብ ባበቋቸው የታሪክ መጻሕፍት የበለጠ ይታወቃሉ፡፡ ‹‹የኤርትራ ጉዳይ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት፣ ተፈሪ መኮንን ረጅሙ የሥልጣን ጉዞ፣ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ታሪክ›› የሚባሉት መጻሕፍት የበለጠ ታዋቂ አድርገዋቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ድርጅትን መሥርተው በኃላፊነት ከመምራታቸው በፊት፣ የቤተ መንግሥት ዘጋቢ የነበሩ ሲሆን፣ ረዳት ሚኒስትር ደረጃ ደርሰዋል፡፡ በዲፕሎማሲው ዓለም ደግሞ በተለያዩ አገሮች በተለያዩ ኃላፊነቶችና በአምባሳደርነት ጭምር አገልግለዋል፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን
ሙሉውን አንብብ-Read More

Jul 12, 2013

የፓን አፍሪካኒዝም ራዕይ ጭንገፋ! (ክፍል ሁለት)

Geez Bet | Friday, July 12, 2013




ዚህ በፊት በጻፍሁት ጽሁፍ ስለ ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ (አመሰራረት) ለማሳየት ሙከራ አድርጊያለሁ። ዛሬ ደግሞ የአፍሪካ ሕብረት እንዴት እንደተመሰረት ትንሽ ካየና በኋላ የፓን አፍሪካኒስቶች ራዕይ እንዴት በአፍሪካ አምባገነን መሪዎች እንደጨነገፈ እናያለን፡፡
    በ1960ዎቹ ብዙ የአፍሪካ ሃገራት ነጻነታቸውን ያገኙበት ነበር፡፡ እነዚህ ነጻነታቸውን የተጎናጸፉ (የተጎናጸፉ የሚለው በምጸት ይነበብልኝ) ሃገራት ዳግም በኢምፔራሊስቶች እንዳይወረሩ የአፍሪካ አንድ መሆንን በየቦታው ማቀንቀን ጀመሩ። በተለይ ኩዋሜ ንኩርማህ አፍሪካ ጠንካራ እንድትሆንና ከውጭ ተጽዕኖ እንድትላቀቅ መዋሃድ አለባት ብሎ ያምን ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የያኔዎቹ መሪዎቹ ካሁኖቹ ጋር ሲወዳደሩ እጅግ ተራመጅ ነበሩ፡፡ በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች የአፍሪካ አንድነትን (ውህደትን) የሚያቀነቅኑ ቡድኖች አጎነቆሉ። ዋና ዋናዎቹ የሚባሉት ቡድኖች የካዛብላንካና ሞኖረቪያ ናቸው፡፡ ሁለቱም ብድኖች የአፍሪካ አንድነት እንዲመሰረት ጽኑ አቋም ቢኖራቸውም፣ እንዴት ነው መመስረት ያለበት የሚለው ጥያቄ ግን የልዩነታቸው ወሰን ሆኖ
ሙሉውን አንብብ-Read More